Sunday, February 16, 2014

የማፊያ ከበርቴዎች በኢትዮጵያ

ነብዩ አለማየሁ

ቢል ጌት ስ  ማይክል ዴል  ማርክ ዙከርበርግ በአልማችንየቢዝነስ ታሪክ በጭንቅላታቸው ፈጥረው      በጭንቅላታቸው ሀብታም የሆኑ የቢዝነስ ሰዎች ናቸው። አስተውላችሁ እንደሆነ  Forbus መፅሄት የአለማችንን ሀብታሞችዝርዝር ሲያወጣ አብሮ የሚወጣ የገንዘቡን  ምንጭና ድርጅት አለ 
ይህንን ሁሉ ያነሳሁት በዚሁ እይታ የሀገራችንን ቢዝንስ እንድናስተውለው ብዬ ነው።
                በኢትዮጵያ አንድ ግለሰብ ወይም  company  ቢዝነሱ የሚሳካው  ወይ ካጭበረበረ ወይም  መንግስት አካባቢ ሰው ካለ  ወይም ጉቦ ከሰጠ ነው።ለነገሩ ዋና ዋናው ቢዝነስ የተያዘው  በህውሀት ሰዎችና ጀሌዎቻቸው ነው። በሌላው ሀገር ተራውን ህዝብ  መንግስት የሚያገለግለው  በታላላቅ የንግድ ተቑማት ላይ ጠቀም ያለ ታክስ በመጣል ነው። እኛ ሀገር ግን በርካታ ከገዢውፓርቲ ጋር  ግንኙነት  ያላቸው በጣም አነስተኛ ታክስ የሚከፍሉና ጭራሽ የማይክፍሉም  ሞልትዋል።
          ኢትዮጵያ ውስጥ  በትክክለኛው መንገድ ታክስ የሚከፍለው የመንግስት ሰራተኛ ብቻ ነው። የኑሮ ጫና ግራ ያጋባው አነስተኛ ገቢ የሚያገኘው በስግብግብ ነጋዴዎች ገንዘብ የሚዘረፈው ሀይ ባይ መንግስት ያጣው ይህው የህብረተሰብ ክፍል ነው። በጣም የሚገርመው  መንግስት በተለያዩ ነገሮች መዋጮ ሲፈልግ እፋጦ የሚቀበለው ይህንኑ የህብረተሰብ ክፍል ነው።  ይህ የህብረተሰብ ክፍል የበይ ተመልካች ሆኖ  ኑሮውን  መግፋት የለበትም በቃ ማለት  አለበት  ።ምክንያቱም ቅኝ መገዛት ከዚ በምን ይለያል።
        የወያኔ መንግስት የሀገሪቱን  የንግድ ህግ እንዳሻው እየለዋወጠ በሀገሪቱ በሌሎች ግለሰቦችና ድርጅቶች የተያዘውን ቢዝነስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የራሱ እያረገ ለ23 ዓመት ዘልቋል። ወያኔ እንደመንግስት  የማያሰራ የንግድ ፍሰት የሚያሰራ የቢዝነስ ህግ በማውጣትና በመተግበር ፈንታ እንደተራ ማፊያ  ሆኖ  ነጋዴዎችንና የቢዝንስ ሰዎችን በማዳከም የራሱን ኤፈርት የተባለ የማይጠረቃ  ድርጅቱን ያጠናክራል። ለምሳሌ በቅርብ ጊዜ ውዲህ የሃገር ውስጥ አስመጪዎችን ናላ አያዞረ ያልው የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሃገሪቱን የንግድ ስርአት አደጋ ውስጥ  ሲጥለው  የህውሀት አባሎችና  ጀሌዎቻቸው ግን ባንኮችን እንደ ግል ካዝናቸው ይጠቀማሉ።  በጣም የሚገርመው ደግሞ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ነጋዴዎች አሰልቺ በሆነው የውጭ ምንዛሬ ወረፋ ለወራት ሲጉላሉ የባንኮች ገዥ ተብልው የሚሾሙት የህውሀት አሻንጉሊቶች  በቲቪ እየቀረቡ የውጭ ምንዛሬ ሞልቶ ተርፉል ይላሉ።
              ከሁሉም በላይ እጅግ በጣም የሚያስገርመው ደግሞ  የዚህ የንግድ ጉዳት    በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ላይ የሚያመጣውን  አደጋ ዞር ብለው ማስተዋል አለመቻላቸው ነው ። በቅርብ ጊዜ እንደሰማነው የህውሀት ማፊያ  መንግስት ሲያያቸው ያላማሩትንና  የወያኔ አባላት ያልሆኑትን በርካታ ድርጅቶች ታክስ አጭበርብራቹሀል ብሎ ሲከሳቸው ሰምተናል ሲጀመር ወያኔ ድርጅቶችን በታክስም ሆነ  በአንፃር ህግ በመጣስ የመክሰስ የሞራል ሆነ የህሊና ብቃት የለውም።  በርካታ የህውሀትና የጀሌዎቻቸው ድርጅቶች ታክስ በማጭበርበር ና ማሀበረሰቡን የሚጎዱ ምርቶችን ለገበያ እንደሚያቀርቡ እናቃለን። ለአብነት ያሀል ከወራት በፊት እንድ የህውሀት  ጀሌ የባሀር ዳሩን ጊዎን ሆቴል  በጥቂት ሺ ብሮች ኪራይ  የግሉ እንዳረገው ሰምተን አዝነናል።
ህውሀት ወያኔ በየትኛውም መልኩ ቢሆን የሀገር መምራት ብቃት የሌለው የወንበዴዎች  ስብስብ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን  የወንበዴዎች  ስብስብ የባሰ ችግር ውስጥ ሳይከተው ልጅ አዋቂ ሳይል ሆ ብሎ ተነስቶ  ማስወገድ አልበት።
          ሞት ለአምባገነኖች  ኢትዮጵያችን ለዘላለም በክብር ትኑር !!!!!!

No comments:

Post a Comment