Tuesday, January 28, 2014

የለውጥ ሀይል ለሆነው ወጣት የተዘጉ ደጆች ይከፈቱ!!!

የለውጥ ሀይል ለሆነው ወጣት የተዘጉ ደጆች ይከፈቱ!!!
ከነብዩ አለማየሁ (ኦስሎ)
በሀገራችን ፖለቲካ አያሌ ክስተቶች ተስተናግደዋል እንደ መልካም ባሃል ልናጎለብተው የሚገቡ በርካታ ፖለቲካዊ አካሄዶች አሉ ከነዚም መካከል ዋናውና ወሳኙ አላማ ያልው ቁርጠኛ ተተኪን ማፍራትና እነኚህን ወጣት ፖልቲከኞችን ወደ ፖለቲካው ምህዳር ማምጣት። ወጣቱ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሀላፊነት እንዳለው እንዲሁም ሀገራዊ ፍቅር ተስፋና ለሚፈጠሩ ለውጦች ወሳኝ የሆነውን ሚና ሊጫወት እንደሚችልና ቁርጠኛ አቋም እንዲይዝ የማድረግ ሀላፊነት ከፖለቲክኞቻችን የሚጠበቅ ወሳኝ ምግባር ነው።


ለአላማውና ለሀገር ፍቅር የቆመን ወጣት ለማፍራት በወያኔ የተሰሩ አልያም እየተሰሩ ያሉ መጥፎ ነገሮችን ብቻ መንገር በቂ አይሆንም ። ምንና እንዴት ለውጥን በምንሻት ሀገራችን ላይ ማምጣት እንዳለብን ማሳየት ሀሳቦችንና ልምዶችን በማጋራት  የተሻለ ነገን በሀገራችን የማምጣት ሀላፊነት በሁላችንም ዘንድ ይጠበቃል።
በሀገራችን ኢትዮዽያ በርካታ በገዥው መደብ እየተሰሩ ያሉ ሀገራዊ ማንነትን ሊሸረሽሩና ሊያጠፉ ሆን ተብሎ የተቀነባበሩ ሴራዎችን በምናይበት ወቅት በለውጡ ሂደት ላይ ወሳኝ ተሳትፎ ያልውን ወጣት ደጃችንን ከፍተን አቅሙ እንዲጎለብትና የወሳኙ  ሂደት ባለቤት ልናደርገው ይገባል  ነተጨማሪም በሃገራዊ ፍቅር በመቻቻልና ከብሄርተኝንት አስተሳሰብ የፀዳና  ወደ ብሄራዊ ስሜት እንዲመጣ የማድረግ ሀላፊነት የያንዳዱ ፖለቲከኛ  ተግባር ነው።
ሀገርን ማአከል አድርገው እየታገሉ የሚገኙ የፖልቲካ ድርጅቶችና መሪዎች  ሁሉ የተዘጉ ደጆቻቸውን የለውጡ ዋና ግብአት ለሆነው ወጣት ብሮቻቸውን  በመክፈት ቁርጠኛ የለውጥ ሀይሎችን በብዛት የማፍራት ሀላፊነት ይጠበቅባቸዋል። በተደጋጋሚ በፖለቲከኞቻን ላይ የሚታየው ግላዊ አመለካከትን በፓርቲና በአባላት ላይ ጭኖ ተግባራዊ የማድረጉ ጉዞ እስካሁን ላለንበት የፖልቲካ ሂደት  ያልበጀንና  የፍላጎታችንም ገደብ ውሰን ላለመሆኑ ማሳያ የሆነን  ተሞክሮነው።
በኢትዮዽያችን ፖለቲካ ለአንዳፍታ ቆም ብለን ስናስብ ሁላችንም በምንታገልላትና በምንሻት ሀገራችን ላይ እጅ ለእጅ ተያይዘን በነፃነትና በዕኩልነት የምንኖርባትን ኢትዮጵያን ለመገንባት ቀደምት ፖለቲከኞቻችን ያለፈውን የትግል ሂደት መልካሙን ከመትፎ በመለየት ለተተኪዎች አስተምሮና አሳይቶ በማፍል የምንመኛውን መልካም ለውጥ መስራት ኣልያም መቀየር ለሚችለው አካል በማስተላለፍ ታሪካዊ ሀላፊነታችንን መወጣት ይገባናል። በዘመናቸው  45 አመትና ከዚያም በላይ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ልክ አይደለም ዛሬ ደግሞ ጊዜው የሚፈቅደው አካሄድ ይሄ ነው ብሎ   የሌላውን የትግል  ሂደት ተስፋ አስቆራጭ ለማድረግ  መሞከር ሃላፊነት ከሚሰማው ለሃገርና ለህዝብ ነፃንት ቆሜያለሁ ከሚል የፖለቲካ ድርጅትና መሪ የሚጠበቅ አስተያየት አይመስለንም። በቅርቡ አቶ ሌንጮ ወደ ሀገር ቤት የመግባት እቅዳቸውን በተመለከተ የሰጡት አስተያየት የሌላውን የትግል  ሂደት ከጥያቄ ውስጥ ለማስገባት  ለማጣጣልና ተስፋ አስቆራጭ ለማድረግ  የተደረገ ይምስለኛል።   ነገር ግን እርሳችው ብቆዩባቸው በርካታ አመታት ውስጥ  ታላቅ የተሰኙ ለችውጦች  በሀገራችን ውስጥ ተከስተዋል በነኚህ ትልግሎች ውስጥ እርሳችው የሚመሩት ድርጅት የለውጡ ባለቤት ያልሆነበትን ምክንያት መመርመር ከዚያም ለተተኪዎች እድሉን መስጠት  በተሻለ መልኩ ለውጡን ሊያመጡ የሚችሉት ሀይሎች ላይ ጊዜን እቅምን በማጎልበት ከመሪነት ወቶ ወይም በጡረታ ተገልሎ በማማክር የስራ ዘርፍ እንደሌላ የትግል ዘርፍ በማየት ሂድቱን ማጎልበት  የሚገባ ሲሆን አልያ በአመራር  ለመቆየት ሲባል በየጊዜው የፖለቲካ ፓርቲዎችንና አጀንዳዎችን ማዘጋጀት ለውጥንና ነፃነትን የናፈቀውን ህዝባችንን ወደዋላ መጎተት ነው። ከምንም በላይ በተለያየ የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥና የትኛው የፖለቲካ ድርጅት እውነት ለሃገራችን ለውጥ ለማምጣት የያንዳንዳችንን አስትዋፆ የሚሻው የለውጥ ሃይል የትኛው ነው ብሎ በማሰብ ላይ ላለው ወጣት ተስፋ አስቆራጭ እንዳይሆን ቆም ብሎ ማስቡ መልካም ነው።


ወጣቱ በአሁኑ ጊዜ  የሚፈልገው ቁርጠኛና ከመሬት የወረደ ትግል ነው። መሪዎቻችን በሀላፊነት መምራትና የለውጡ ሀዋርያ እንዲሆን ደጆቻችንን ከፍተን ታሪካዊ ሃላፊነታችንን ታሪክ በመስራት እንወጣ::

Friday, January 24, 2014

Mr Bekele Gerba a Lecturer in Addis Ababa University and prisoner of conscience has completed his 3 year imprisonment a week ago nonetheless, Ethiopian Government didn't release him so far. Where are Human Rights Watch BBC News CNN International Reuters Al Jazeera English The Stream FRANCE 24 EnglishAllAfrica.com AFP news agency CBC Egypt Ancient Egypt News Humanity's Team? Please use the following #hashtagunder all your status updates, pictures, and comments to show your solidarity with humanity!

Thursday, January 23, 2014

አምባገነናዊ ሥርዓት “ህጋዊ” የሆነባት ሀገር - “ኢትዮጲያ”
=====================================
በናትናኤል ካብቲመር ኦስሎ ኖርዌይ January 21, 2014

አምባገነናዊ ስርዓት መሰረታዊነት በጎደለው ንድፈ ሃሳብ ላይ የተመረኮዘ የሃገርንና የህዝብን ችግሮች ከመፍታት ይልቅ የስርዓቱን እድሜ ለማራዘም ሆን ተብሎ በተቀረፁ ፖሊሲዎች የታጀለ ፣ የጥቂቶችን ብቻ መብትና ጥቅም የሚያስከብር አፋኝ ስርዓት ነው። በአንፃሩ ደግሞ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የአንድን ማህበረሰብ ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ፣ የሁሉን ዜጋ መብት አክብሮ በማስከበር እንዲሁም በእኩል አይን በማየት ፣ የተለያዩ ሁለንተናዊ የዘላቂ እድገት አማራጮችን ለብዙሃኑ በሚጠቅም መልኩ ሥራ ላይ በማዋል የሚል መሰረታዊ ንድፈ ሃሳብ ላይ የሚመሰረት ፣ የሃገርን እድገትና ልማት ለዘለቄታው አረጋግጦ ለዜጎችም የተሻለ የኑሮ እድል የሚፈጥር ስርዓት ነው።

በአለማችን በተለያዩ ሃገራት ያሉ አምባገነናዊ መንግስታት ፖለቲካዊ አወቃቀራቸውን ዲሞክራሲያዊ ለማስመሰልና ህዝባቸውንም ሆነ ሌሎች መንግስታትን ስለስርዓታቸው ዲሞክራሲያዊነት ለማሳመን ሲጥሩ የወያኔ መንግስት ግን አምባገነናዊ ስርዓት በህዝብም ሆነ በተለያዩ መንግስታት ህጋዊ ተቀባይነት እንዲያገኝ በድፍረት ሲደክም ይታያል። ላይ ላዩን ዋናው ጠላታችን ድህነት ነው እያለ አምባገነናዊ ከሆነ የፖለቲካ ስርዓት የመነጨውን ለወያኔ ካምፓኒዎች ብቻ ተመቻችቶ የተቀመረ የተሳሳተ ኢኮኖሚያዊ አወቃቀር በማራመድ የኑሮ ውድነቱን በማናር ከዛሬዎቹ በተጨማሪ የነገዎቹን ብዙ ድሀዎች በመፍጠር ላይ ይገኛል።

የወያኔ መንግስት አፈቀላጤዎች እየተቀባበሉ እንደሚወተውቱት ለህዝቡ ከዲሞክራሲ ይልቅ ሰላም የሚሉት ዘይቤ ተጨባጭነቱ አጠያያቂ መሆኑ ግልፅ ነው። ምክንያቱም የዜጎችን መብት በመርገጥ እና በጉልበት የመብት ጥያቄዎችን በማፈን የሚመጣ የይስሙላ ሰላም ዘላቂና አስተማማኝ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ውስጥ ውስጡን የበረከተ ጥላቻ ፣ ቅሬታና ቂም በመፍጠር ለመጪው የሀገር ሰላምና አንድነት መሰረተ ሰፊ ስጋት መሆኑ አሌ የማይባል ሐቅ ነው።
የወያኔ መንግስት ከጫካ ጀምሮ ወጥ የሆነ ፖለቲካዊ ስርዓትን ለመገንባት ከመሞከር ይልቅ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ሀገራትን የፖለቲካ ስርዓት እያጣቀሰ አንዴ እንደዚህኛው ሀገር ሌላ ግዜ ደግሞ እንደዛኛው ሀገር አይንት ስርዓት እንገነባለን እያለ እድሜውን ሲያራዝም ቆይቷል። በስልጣን ቆይታውም ስርዓቱ የፈጠራቸውንና የሚፈጥራቸውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን በግልፅነት ለይቶ ከማውጣትና በተገቢው መንገድ ከመፍታት ይልቅ በማድበስበስና በማቃለል ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ የስርዓቱን መልካምነት በመስበክ አምባገነናዊነቱን ተቀባይነት እንዲያገኝ ሲጥር ይስተዋላል።

ምዕራባዊያንም ሆኑ ሌሎች በርካታ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የሰፈነባቸው የአለማችን ሀገራትን እንደምሳሌ ወስደን ለምን አምባገነናዊ ስርዓትን አስወግደው ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመግንባት ለዘመናት ታገሉ? የሚል ጥያቄ ብናነሳ መልሱ ቀላል ነው። ለአንድ ሀጋር ዘላቂነት ያለው ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ለማምጣት የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ብቸኛው አማራጭ ስለሆነ ነው። በሀገራችንም ያለውንም ሞልቶ የፈሰሰ ዘርፈ ብዙ ችግር ለመቅረፍም ይህንኑ አማራጭ መከተል ብቸኛ መፍትሄ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም።

በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ ማህበራት ምንም እንኳን ዝርዝር የፖሊሲ ቀረፃና የትግል አቅጣጫቸው ለየቅል ቢሆንም የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የኢትዮጲያን ስር የሰደደ ችግር መፍትሄነቱን ጥያቄ ውስጥ የሚከት የለም። ይህንንም ስርዓት ተመራጭ ያደረገው ነባራዊዎቹን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን ከመፍታቱም ባሻገር ዳግም እንዳይፈጠሩ መከላከሉ ፣ የሰው ልጆችን ሁሉ እኩል አድርጎ ማየትና መብታቸውንም በእኩልነት ማክበር እንደመሰረታዊ መርህ መከተሉ ነው።

በአሁኑ ግዜ የሰው ልጆችን የሚያበላልጡና እኩልነቱን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ ለምሳሌ እንደዘውዳዊ አገዛዝ ዘመን በእግዚአብሔር ለገዢነት የተመረጠ ዘር ብሎ መለየት እንዲሁም እንደ ባሪያ ፍንገላ ዘመን ነጭ ከጥቁር የሚሻል ነው ማለትና የመሳሰሉት ነገሮች ከህጋዊነት ውጪ ሆነዋል። ነገር ግን በሀገራችን ኢትዮጲያ ቅርፁን በለወጠ መልኩ የሰው ልጆችን መሰረታዊ የእኩልነት መርህ የሚጥስ የስልጣንና የጥቅም አድሎ “ያለፈውን ስርዓትለመጣል ስለታገሉ” ወይም “የምንትስ ዘር ስለሆኑ” ተብሎ የህዝብ አገልጋይነት ላይ ማተኮር የሚገባውን የመንግስት ስልጣን እንደ ውለታ መመለሻና ኩርፊያ ማባበያ በስጦታ መልክ የማበርከት በግልፅ የሚነገርና የሚታይ ፀረ ዲሞክራሲያዊ ኩነት በመከላከያና በተለያዩ የመንግስት አካላት ተንሰራፍቶ ይታያል።

በጥቅሉ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ተግባራዊነቱ የሚጀምረው “በብዙሃኑ” (majority) የተወደደውንና የተመረጠውን የፖለቲካና ኢኮኖሚ አመለካከት የስልጣን ባለቤት በማድረግ ፣ “በብዙሃኑ” (majority) እና “በአናሳው” (minority) መካከል ህጋዊነት የተላበሰ የተቻቻለ የአገዛዝ ስርዓት በመፍጠር ፣ “ብዙሃኑ” ና “አናሳው” የሚባሉትን ወገኖች በፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አማራጭ አመለካከታቸው ብቻ በመለየት ነው።

የሀገራችን አምባገነን መንግስት ግን “ብዙሃኑ” ና “አናሳው” የሚባሉትን ወገኖች ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አማራጭ አመለካከታቸው ይልቅ ከዘርና ብሔር ጋር አቆራኝቶ የስርዓቱን ዲሞክራሲያዊነት ይሰብካል። ክቡር የሆነውንና የማንነት አይነተኛ መገለጫ የሆነውን ብሔር ባልተገባ መልኩ የጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅምን ከማስከበር አንፃር ሲመነዝረው ይስተዋላል። ብሔር መሰረታዊ ከሆኑት የማንነት መገለጫዎች የተከበረውና ዋነኛው መሆኑ አጠያያቂ ባይሆንም ከፖለቲካና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ጋር የሚኖረው ቁርኝት በጥንቃቄና ግልፅ በሆነ መልኩ ሀገርን በዘላቂነት ከሚጠቅምና የዜጎችን ተጠቃሚነት ከሚያረጋግጥ አማራጭ የፖለቲካ ንድፈ ሀሳብ ሳይዋቀር እንደ ህወሃት ዛሬን ለማለፍ እንደነገሩ ለየብሄሩ ተሰርቶ ከተለጠፈ ወደፊት ከሚፈጥረው አስከፊ አደጋ ባሻገር ሀገራዊ ስሜትን በዘላቂነት ያኮስሳል።
የወያኔ መንግስት ከማንኛውም መንግስት እንደሚጠበቀው ለዜጎች ህልውናና ደህንነት አፅንኦት በመስጠት ምሳሌ በመሆን ለህግና መሰረታዊ መብቶች የዳበረ ክብር ያለው ፣ ለሀገሩ ስር የሰደደ ጥልቅ ፍቅር ያለው ማህበረሰብ ከመፍጠር ይልቅ አምባገነናዊ ስር አቱን በይስሙላ ህግጋት ለመደገፍ እንደ ፀረ ሽብር አይነት ህጎችን ለጊዜያዊ የስልጣን ጥቅም ሲባል በማጣመም ስርዓቱን የተቃወሙትን ሁሉ እንደወንጀለኛ በመፈረጅ ማሰሩን አማራጭ ሃሳቦችን በግልፅ ማፈኑን ስራዬ ብሎ ተያይዞታል። ለስልጣን ጥምና ቆይታ ካፀደቃቸው የተሳሳቱ ፖሊሲዎች የተለዩ ምክንያታዊነት ያላቸው አማራጭ ሀሳቦችን የሚያመነጩ አካላትን እንደ ሀገርና ህዝብ ባላንጣ በመፈረጅ የሰከነ ውይይት ከማድረግ ይልቅ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እንደመሰረት ድንጋይ የሚያገለግሉ የተለያዩ የፖለቲካና የሲቪክ ማህበራትን እንዲሁም የተለያዩ የነፃ ሚዲያ ተቋማትን በማፈራረስና ከሃገር በማባረር የተቀሩትንም ወደ ስርዓቱ መጠቀሚያነት በግድም ሆነ በማባበል በመለወጥ ስልጣን የህዝብ የሚሆንበትን ቀን እያራቀ ይገኛል።የድርጊቱን ፀረ ዲሞክራሲያዊነት እንዲሁም የህጉን የአተረጓጎም መጣመምና መፋለስ ጥያቄ ሲነሳ የህጉን ከሌሎች ሀገራት ህግጋት ጋር ያለውን ተመሳሳይነት ብቻ በመደጋገም ዋና ጥያቄ የሆነውን የህጉን የአተረጓጎም ጥመት አድበስብሶ ያልፋል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህም የዚህ አፋኝ ስርዓት ቀጥተኛ ተጠቃሚና አቀንቃኞች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች መንግስታቸውን በማሞካሸት አምባገነናዊ ስርዓቱ ህጋዊ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሲሰብኩ ማየት የተለመደ ሆኗል። ዘላቂ የሆነ የዲሞክራሲና የኢኮኖሚ እድገት የሚያረጋግጡ አማራጭ ሀሳቦች የሚያቀርቡ አካላትን በአደባባይ እየዘለፉ በግልፅ የሚታየውን የመብት ረገጣና ከመጠን ያለፈ የኑሮ ውድነት ችላ በማለት ስለመንግስታቸውን ቅዱስነት አይናቸውን በጨው አጥበው ይሟገታሉ። አማራጭ የፖለቲካ አስተሳሰብ አቅራቢ አካላትን በፅንፈኝነት በመፈረጅ ጥቃቅን ችግሮቻቸውን በማግዘፍ የወያኔ መንግስትን ፍፁም ዲሞክራሲያዊነት ለማሳመን ይታትራሉ። “ሌሎች ሃገራት እንደምሳሌ የሚጠቀሙበት መንግስት አለን” ብለው በድፍረት ይናገራሉ። በተለያዩ የምዕራባዊ ሃገራት የሚኖሩ የወያኔ ደጋፊና አባላት በሚኖሩበት ሀገር ያለውን የጎለበተ የዲሞክራሲ ስርዓት የፈጠረውን የህግ የበላይነትና የዜጎች መብት መከበር በጎ ገፅታ እያዩ እንኳን አቋማቸውን ማስተካከልና ያንኑ ለሃገራቸው መመኘት ሲገባቸው የኑሮ ውድነት ያጎበጠው የሃገራችን ህዝብ ጫንቃ ላይ የተጫነው አምባገነናዊ ስርዓት “ፍፁም” የሆን መልካምነት ሽንጣቸውን ገትረው ይሟገታሉ። በተወሰነ መልኩ እንኳን በጎ የሚባሉትን የፖለቲካና ኢኮኖሚ ገፅታዎች በሃገራችን ይፈጠር ዘንድ እንደ አስተያየት ከመጠቆም ይልቅ አምባገነናዊ ስርዓቱን የማይሳሳት ፣ ሁሉን ያሟላና ቀጥተኛ ብለው አፋቸውን ሞልተው ይናገራሉ።

የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መጀመር ሀገራችንን ለዘመናት ከተቆራኛት የችግር ደዌ ከማላቀቅ አልፎ ዘላቂ የሆነ መሰረታዊ መብቶች መከበርና ለህግ የበላይነት መስፈን ይረዳል። የኢትዮጲያ ህዝብም ይህንን በሚገባ ያምናል ፣ ያውቃል ፣ የስርዓቱንም አስፈላጊነት በምርጫ 97 ወቅት አደባባይ ወጥቶ ጠይቋል። ያሉበትንም ዘርፈብዙ ችግሮች በአስተማማኝ መልኩ ለመፍታት አምባገነናዊ ስርዓትን በማስወገድ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን በመገንባት መሆኑን አውቆ ተረድቷል። ነገር ግን የወያኔ መንግስት የዲሞክራሲያዊ ስርዓት በመገንባት ሂደት ውስጥ መሰረታዊ ሚና የሚኖራቸውን ህዝባዊ አንድነት ኃይልና መሰረቱ የጠነከረ የትብብር ፖለቲካ እንዲዳከምና ዳግም እንዳይፈጠር ሌት ተቀን በማሴር ፣ ተሳታፊዎቹንም በማሰርና ከሀገር በማባረር በጉልበተኝነት የህዝብን ድምፅ አፍኖ አስቀረ። ብሎም መሰረታዊ ፣ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብትን አክብረው የሚያስከብሩና እውነተኛ የሆነ ሁለንተናዊ የሀገር እድገት ለማረጋገጥ ተግተው የሚሰሩ የዲሞክራሲ አርበኞችን ከመፍጠር ይልቅ የህዝባቸው ችግርና መብት መረገጥ የማይጎረብጣቸው አምባገነናዊውን ስርዓት አምላኪ ወገንተኛ ግለሰቦችን እንደ ህዝብ ተወካይ በመመልመል በ 2002 ምርጫ 99.6 በመቶ አሸነፍኩ ብሎ በሚያሳፍር ድፍረት ተናገረ።

ይዘገይ ይሆን ይሆናል እንጂ በህዝብ ፈቃድና ይሁንታ ተመርጦ የህዝብ አገልጋይ የሚሆን ዲሞክራሲያዊ መንግስት የመፈጠር አይቀሬነት ሁላችንም እናውቃለን። የህግ የበላይነት ፣ የግለሰብም ሆነ የብሄር መብት እንዲሁም ክብር ፣ ዘላቂነት ያለው ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እድገት የሚረጋገጠው አምባገነናዊውን ስርዓት ተወsግዶ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሲገነባ መሆኑንም እናምናለን። ይህም እውን ይሆን ዘንድ ጠንክረን እንታገላልን።
በአምባገነኖች ውድቀት ላይ ዲሞክራሲያዊነት ይለመልማል !!

Sunday, January 19, 2014

ዴሞክራሲ ከማን ይጠበቃል??

 ከ ነብዩ አለማየሁ ኦስሎ ኖርዌይ   
           ዴሞክራሲን ለማምጣት እርስ በእርስ መደማመጥና ሃሳብን በነፃ ማንሸራሸርን ይጠይቃል ይሄ ዋና መሰረታዊ ነገር ንው።እስቲ የሀገራችንን ነባራዊ ሁኔታ እንዳስ በኢትዮዽያ የህውሀት መንግሥት አመጣጡ እንደኔ ዓመለካከት ጥቂት የትግራይ ገበሬ ልጆች በኤርትራ የሻብያ እንቅስቃሴ በማየት ለምን እኛስ ሀገራችንን ትግራይን ነፃ አናወጣም ብለው ነፍጥ ይዘው ጫካ ገቡ በጊዜው የደርግ መንግስት በብዙ ሀገር ወዳድ ኢትዮዽያዊያን የተቀጣጠለውን ዘውዳዊውን ስርኣት አስወግዶ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሲውተረተር የእንዚህ ጥቂት የዘረኝነት ዐባዜ የተፀናወታቸው ጥቂቶች ኣላማቸውን ለማሳካት ኣመቺ ጊዜ ተፈጠረላቸው በተጨማሪም በወቅቱ ሿብያ በኤርትራ በኩል ያድርገው የነበረው ጦርነት የደርግን አትኩሮት በተሻለ መልኩ መሳቡ ተመቻቸው በሶማልያ በኩል የሚካሄድውም ጦርንት ሌላው ምቹ ኣጋጣሚን ፈጥሮላቸው ነበር።

  እነዚህም የትግራይ ልጆች በዙ ተባዙ በትግራይም ጫካዎች ውስጥ ተሰባሰቡ ነገር ግን በህልምም ይሁን በውን በኢትዮዽያ ዴሞክራሲን ለማስፈን የህግ የበላይነትን ለማስከበር ኣላማ አልነበራቸውም በጭራሽ ኣላማቸው ኣንድ ና ኣንድ ነበር የትግራይ ህዝብ ነፃ ኣውቺ ነበሩ ከእነርሱ ዴሞክራሲን መጠበቅ የማይታስ ነው።
        የእውንቱ ሌላው እይታ በትግራይ ጫካ የበዙት የቀድሞው ታጋዮች የደርግ መዳከም ምቹ አጋጣሚ ፈጠረላቸው ተከዜን ተሻገሩ ያኔ ኢትዮጵያን መቆጣጠር እንደሚችሉ ሁኛ ሰው ከወደ UN ሹክ ኣላቸው ያኔማ ለኣማራው ፥ ለኦሮሞው  ፥ ለቤሄሩ ሁሉ ተወካይ ፈላልገው ካገኙ ቡሃላ ሰተት ብለም ገቡ ።            በስልጣን ለመቆየት አንዱን ብሄር ከሌላው ማጋጨቱን ተያያዙት ከዚያም እነርሱ የተዋደቁለትን ዐላማ ማራመድ ጀመሩ የሃገሪቱን ዋና ዋና ድርጅቶች ወደ ግል ይዞታነት በማዘዋወር ሰበብ ወሰዱ ትልቅ የቢዝነስ ኢምፓየር አቋቋሙ ለኢትዮዽያ ህዝብም የይስሙላ ህገ መንግስት ጣል ተደረገለት  እንርሱ ቀጠሉ መሠሎቻቸውን አምጥተው በመሀበር ቤት ስም ና በኮንዶሚኒየም ስም ከተሙ።
hailemariam and samora
ኢትዮጵያ ያሉ ጥቂት ጋዜጦችና ፓርቲዎች ዴሞክራሲን እንፈልጋለ ሲሉ እሺ ይታሰብበታል በማልት ስራቸውን ቀጠሉ የሃገሪቱዋን መሬት ለበዓድ ሸጡ ተከታዮቻቸውን በሃገር ውስጥና በውጪ ልከው አስተማሩ ኣላማቸውን የሚያሰናክልና ከእንርሱ ሃሳብ ውጪ የሆነውን ሁሉ ኣሰሩ ዓልያም ከሀገር አስወጥተው ለስደት ዳረጉት ዋናውን ዓላማቸውን ኣልሳቱም የራሳቸውን ሰዎች ኑሮ ማሻሻልና በኢትዮዽያ የበላይ ሆኖ መታየት። እኛም ኧረ ዴሞክራሲ ኧረ ነፃነት ኣልን ወይ ዴሞክራሲ ዓንዳንዶቹ እንዳውም ዴሞክራሲ ከፈለጋችሁ ጫካ ግቡ ማለት ጀመሩ በዚ መሃል ባዘጋጁት ምርጫ በተገኘች  ትንሽ ክፍተት ያኔ የኢትዮዽያ ህዝብ እንድሚጠላቸው ግልብጥ ብሎ ውጥቶ ኣሳያቸው ከዚያም ገድለውም ኣስረውም ገርፈውም ቢሆን ካረጋጉ ቡሃላ በውንም ይሁን በህልም ይህ ኣይነቱ ስተት ዳግመኛ እንደማይደገም ቃል ገብተው እስከ መጨረሻው ጭላንጭሉን አዳፈኑት።

   ሀይልማርያም ጠቅላይሚንስትር ሆነ ያኔ ከጀርባ ሆነው ኢኮኖሚውን ፥ መከላከያውን ፥ ደህንነቱንና ውጪጉዳዪን ህውሀቶች በመቆጣጠር እኛ ዴሞክራሲያዊነን በህጉ መሰረት የስልጣን ርክክብ ዓደረግን ኣሉን ታድያ እውነት ከነኚህ የምንሻውን ዴሞክራሲ የሠፈንባት  እኩልነትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ኢትዮዽያን ከህውሀት  መጠበቅ የዋሀንት ነው ። ካለን ተሞክሮ እናም እንደኔ ሃሳብ ስልኛ ነፃነት ከኛ ሌላ ሊጮህልን የሚችል የለምና ልዩነታችንን አቻችለን ሁላችንም በትግላችን እንፅና።





Thursday, January 16, 2014

28 Ethiopian political and civic organizations sent a protest letter to the UN


The Ethiopian Borders Affairs Committee sent a letter to the United Nations Secretary-General, H.E. Mr. Ban ki-Moon exposing the TPLF/EPRDF secret border deal with the Sudan and rejecting any attempt that violates upon the sovereignty and territorial integrity of Ethiopia. The protest letter has been endorsed by 28 Ethiopian political and civic organizations according to The Ethiopian Borders Affairs Committee.
Ethiopian Border Affairs Committee
P. O. Box 9536 Columbus, Ohio 43209 USA
E-mail: ethiopianborders@gmail.com
H.E Mr. Ban Ki-Moon
United Nations Secretary General
1st Avenue, 46th Street
New York, NY 10017
January 10, 2014
Your Excellency:
We, the undersigned representatives of various Ethiopian political parties, civic organizations and professional associations, have the honor to bring to your attention our strong protest against the secret border deal that the dictatorial governments of Ethiopia and the Sudan have recently been hatching.
The respective territorial limits of both countries were defined by the Anglo-Ethiopian Treaty of 1902 at the turn of the last century when Great Britain was the colonial power administering the Sudan.  As is customary in international practice in delimiting national boundaries, the treaty provided for the setting up of a Joint Boundary Commission to be appointed by both sides to carry out the actual demarcation of the boundary on the ground. Upon completion of the demarcation process both parties were required to notify their citizens of the boundary as demarcated.
Despite the clear mandate of these undertakings, however, the treaty has remained a dead letter for over a century and, as a consequence, the boundary between the two countries has never been demarcated by a joint commission. Instead, contrary to both the spirit and letter of the provisions of the treaty, Great Britain appointed its own officer, Major Charles W. Gwynn, to unilaterally and arbitrarily demarcate the boundary without the knowledge and the participation of Ethiopian boundary commissioners. In the event, the demarcation line which resulted from this high-handed exercise greatly favored the Sudan while causing Ethiopia to suffer a corresponding amount of territorial loss.
Notwithstanding the fact that the demarcation of the boundary by one of the Contracting Parties cannot legally bind the other, nevertheless Sudan has over the years importuned successive Ethiopian administrations to accept the validity of the unilateral demarcation undertaken by the British.  The consistent and unequivocal response of these administrations, however, has been to reject the validity of Sudan’s claims, calling instead for a negotiated settlement of the boundary on the basis of the original treaty with the full knowledge, participation and consent of peoples likely to be affected by the demarcation line.
As Your Excellency well knows, the international political system grants a considerable degree of importance to rights in respect of territory. The function of a boundary between states is the attribution of territory and, thus, the extent of a state’s territorial sovereignty. When the extent and limits of a state’s territorial sovereignty are determined solely and arbitrarily by one state to the detriment of the other, however, the boundary so determined becomes an enduring source of friction and tension between the adjoining states. It is precisely to avoid such a result that international law attributes to an international boundary a compelling degree of continuity and finality. Nevertheless, this venerable principle will be respected and observed in practice only if the given boundary was established in accordance with law. More importantly, a boundary regime can be regarded as final only where either of the states can clearly establish its legal credentials.  In the case of the Ethio-Sudan boundary, this means that the treaty regime set up by the parties – and no other arrangement- was meant to govern the boundary and title to territory.
According to media reports originating in the Sudan, however, under the just-concluded secret deal between the President of the Sudan and the Prime Minister of Ethiopia, huge swathes of our ancestral lands will be ceded to the Sudan.  These reports have been received with utter shock, resentment and anger by Ethiopians at home and abroad.  Neither the current generation of Ethiopians nor those of future generations will allow the deal to stand for it constitutes a serious violation of the treaty regime set up at the turn of the century and holds for naught the sacrifices of past generations of Ethiopians to preserve the territorial integrity of their country.  We wish to add that thousands of our people will be forced to lose their homes, farms and investments if the border deal is implemented without their participation and consent.
We are not unmindful that members of the United Nations and their sitting governments like those of the Sudan and Ethiopia are clothed with a certain degree of legitimacy in the eyes of international law and politics, even as such legitimacy deprives ordinary citizens adversely affected by the decisions of those who rule them legal standing and recourse in such matters. And yet the actions of these officials who purport to speak in their behalf are bereft of any legitimacy in the eyes of the very populace whose interests they claim to represent. This is particularly true when it concerns highly sensitive and emotionally charged questions of territorial sovereignty.  As such, the border deal of today hatched by unelected elites will be the ticking bomb of tomorrow.   Since it has neither support in law nor received the consent of the Ethiopian people, it will fester as a major source of friction and tension between the brotherly peoples of Ethiopia and the Sudan. Needless to add, the Horn of Africa region does not need an additional source of insecurity and instability beyond those that already plague the region. Accordingly, we wish to entreat Your Excellency to use your good offices to any extent appropriate and possible so as to forestall the dangerous situation the border deal is otherwise most likely to engender now or in the future if it goes into effect.
In any case, we would like to go on record as asserting our right to territorial sovereignty as defined by treaty – and not any other agreement that is reached behind the back of the Ethiopian people. We reserve the right to not honor any boundary that results from the agreement of an unelected government that is devoid of any support or legitimacy among its own people. In closing, we would like Your Excellency to know that the current extremely narrowly- based government of Ethiopia and the similarly discredited government of the Sudan are grasping at straws by using the border deal as a way of ensuring their political survival by a mutual exchange of promises foreswearing the use of their territories by organized movements seeking to overthrow their respective governments. This survival instinct underlies the parties’ desire to make a border deal and to keep it from public scrutiny without consideration of its impact on the people of Ethiopia.
Please accept the assurances of our highest consideration.
Sincerely,
  1. Ethiopian Border Affairs Committee (EBAC)
  2. Ethiopian People’s Congress for United Struggle (Shengo)
  3. Ethiopian People’s Revolutionary Party-Democratic (EPRP-D)
  4. Ethiopian Medhin Democratic Party (Medhin)
  5. All  Ethiopian Socialist Movement (ME’ISONE)
  6. Ethiopian People’s Patriotic Front (EPPF)
  7. Amara Democratic Movement Force (ADMF)
  8. Ethiopian Democratic Hibrehizb Unity Movement (EDHUM)
  9. Tatek Movement for Freedom, Democracy and Unity for Ethiopia
  10. Tigrean Alliance for National Democracy (TAND)
  11. Oromo Liberation Front (OLF)- led by General Kamal Galchuu
  12. Ethiopian National Transitional Council (ENTC)
  13. Moresh Wegenie Amara Organization (MWAO)
  14. The Legitimate Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Exile
  15. Gasha for Ethiopians
  16. Ethiopiawint: Council for the Defense of Citizens Right
  17. Beruh Ethiopia Democratic Movement
  18. Ethiopian Civic Consortium in UK
  19. Solidarity Committee for Ethiopian Political Prisoners – Canada (SOCEPP-Can)
  20. Ethiopian Civil Society Support Group in London, Ontario
  21. Anuak Justice Council
  22. Dallas Support Committee
  23. Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE)
  24. Democracy For Ethiopia Forum in San Jose
  25. Ethio-Canada Democratic Forum in Ottawa
  26. Ethiopian Public Forum in Columbus, Ohio
  27. Mahdere Andinet Ethiopian Association
  28. Ethiopian Public Forum in Seattle, Washington
CC.
Embassy of the Republic of the Sudan
2210 Massachusetts Ave. NW
Washington, DC 20008
Dr. Nkosazana Dlamini Zuma
Chairperson of the African Union Commission
P. O. Box 3243
Roosvelt Street
(Old Airport Area)
W21K19
Addis Ababa, Ethiopia
Fax: 251-11-551-7844