Tuesday, December 15, 2015

የህወሃት እና የሱዳን ግንኙነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያለመ ነው። ”የአገሪቱ በጀት 100% ለመከላከያ ቢውልም አይበቃንም” አልበሽር ”ሱዳን 70% በጀት ለመከላከያ እና ፀጥታ ታውላለች” በሱዳን የእንግሊዝ አምባሳደር አሮን (ጉዳያችን ዜና)


የህወሃት እና የሱዳን ግንኙነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ያለመ ነው። ”የአገሪቱ በጀት 100% ለመከላከያ ቢውልም አይበቃንም” አልበሽር ”ሱዳን 70% በጀት ለመከላከያ እና ፀጥታ ታውላለች” በሱዳን የእንግሊዝ አምባሳደር አሮን (ጉዳያችን ዜና)
ከትናንት በስቲያ እሁድ ታህሳስ 3/2008 ዓም በሱዳን አየር ኃይል ማዘዣ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት አልበሽር ሱዳን ወደ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ መሸጋገር አለባት ብለዋል።ከእዚህ በተጨማሪም እጅግ በፈጣን ሁኔታ የሱዳንን ደህንነት ሊያስከብር የሚችል የአየር ኃይል መገንባት አለብን ብለዋል።የሱዳኑ ፕሬዝዳንት አገራቸው ለመከላከያ የምታወጣው በጀት በዝቷል የሚሉ ተቺዎቻቸውን በቁጣ ተናግረዋል።በመቀጠልም ”በዙርያችን ያሉ ፀጥታቸው የተናጋ አገሮችን ተመልከቱ። የአገሪቱ በጀት 100% ለመከላከያ ቢውልም አይበቃንም።የእራሳችን የጦር መሳርያ ፋብሪካ ያስፈልገናል….እጅግ በፈጠነ ሁኔታ ትልቅ አቅም ያለው የአየር ኃይል መገንባት አለብን” ብለዋል ፕሬዝዳንት አልበሽር።በሌላ በኩል በሱዳን የእንግሊዝ አምባሳደር አሮን ”አሲያስ” ለተሰኘ ጋዜጣ ሲናገሩ ”የሱዳንን ዕዳ መቀነስ ፈፅሞ አይታሰብም።ምክንያቱም እስከ 70% በጀት ለመከላከያ እና ለፀጥታ ጉዳይ እንጂ ለሌሎች የልማት ዘርፎች እንደ ትምህርት፣ጤና ለመሳሰሉት አታወጣም።” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት አልበሽር ባለፈው ሳምንት ጋምቤላ ኢህአዴግ/ህወሃት ”የብሔር ብሔረሰቦች በዓል” የብሔር ብሔረሰቦች እስር ቤት ባደረጋት አገር በከፍተኛ ደረጃ የአገሪቱን ገንዘብ በሚያባክንበት ዝግጅት ላይ ተገኝተው ምሽቱን አዲስ አበባ መመለሳቸው እና ከህወሃት ባለስልጣናት ጋር መገናኘታቸውን የሱዳኑ ”ሱዳን ትሪቡን” መዘገቡ ይታወሳል።በአሁኑ ወቅት ህወሃት እና የሱዳን መንግስት የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ በሚሰጥ እና ሕዝብን፣አገርንና ታሪክን በሚያዋርድ መልኩ በኢትዮጵያ ላይ በጥምር ሴራ እየሸረቡ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው።ህወሃት የኢትዮጵያ ህዝብን አንድነት በሚያናጋ መልኩ ጎሳ ከጎሳ የማጣላት እና ከውስጥ ሆኖ ኢትዮጵያን የማዳከም ሥራ እየሰራ ለመሆኑን ብዙ እማኞችን መጥቀስ ይቻላል።በአገሪቱ ላይ የታወጀው የጎሳ ፌድራሊዝም ለ25 ዓመታት ያክል ኢትዮጵያን ሰላም የነሳ መሆኑ እየታወቀ እና ውጤቱም በኦሮምያ እና በሌሎች ቦታዎች የበለጠ ፀጥታ የነሳ መሆኑ እየታየ ለችግሩ የበለጠ ”ቤንዚን የማርከፍከፍ” ሥራ አሁንም በህወሃት እየተፈፀመ ነው።በሰሜን ጎንደር የ”አማራ እና የቅማንት” ሕዝብ በሚል ሕዝቡን የመከፋፈል ‘መንግስታዊ የዘር ፍጅት’ እንዲፈፀም መደረጉን እና እስካሁን ከአንድ መቶ በላይ ሕዝብ ማለቁን ኢሳት ራድዮ በታህሳስ 4/2008 ዓም ከአካባቢው ያነጋገራቸውን ነዋሪዎች ጠቅሶ ገልጧል።
የእዚህ የ”አማራ እና የቅማንት” ሕዝብ በሚል የመከፋፈል ሥራ ላይ የሱዳን የሞራልም ሆነ የገንዘብ ድጋፍ ከወያኔ ጋር ሊኖርበት እንደሚችል የብዙዎች ጥርጣሬ ነው።ሱዳን ሰፊ የሆነውን የኢትዮጵያ ለም መሬት እና ወንዞች ወደ ግዛቷ ለማካለለ ከህወሃት ጋር መስማማቷ እና ሰሞኑን ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚችል ሲገለጥ ነው የሰነበተው። ዛሬ ታህሳስ 5/2008 ዓም በዋሽንግተን ኢትዮጵያውያን በሱዳን ኢምባሲ በር ላይ የድንበር ውሉን በመቃወም ትልቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment