Sunday, May 25, 2014

ያለ በቂ ማስረጃ በሕገ ወጥ መንገድ ከአራት ሳምንት በፌት ከተያዙት ስድስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን በተጨማሪ በአንድ ጦማሪ አባል መኖሪያ ቤት ላይ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ


Zone9
ያለ በቂ ማስረጃ በሕገ ወጥ መንገድ ከአራት ሳምንት በፌት ከተያዙት ስድስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን በተጨማሪ በአንድ ጦማሪ አባል መኖሪያ ቤት ላይ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ፡፡Zone 9 bloggers
በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ በዞን ዘጠኝ ጦማሪና መስራች ሶልያና ሽመልስ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ፖሊስ ብርበራ ያካሄደ ሲሆን የጸረ-ሽብር ሕጉ ይፈቅድልናል የሚል ምክንያት ሰጥተው ያለ ፍርድ ቤት የብረበራ ማዘዣ ከካሜራ ቀራጭ ጋር የተገኙት ሰባት ፖሊሶች በጦማሪዋ ክፍል እና ሌሎች አስፈላጊ ነው ባሉዋቸው ክፍሎች ሲያካሂዱ ነበረውን ብርበራ ጨርሰው ይጠቅመናል ያሉትን የዶ/ር መረራ ጉዲና የመጨረሻ መጽሀፍ እና ሌሎች ወረቀቶች ወስደው ቤት ውስጥ የነበሩትን የጦማሪዋን ወላጅ እናት አስፈርመው ከጠዋቱ 4 ሰአት አካባቢ ቤቱን ለቀው ወጥተው ነበር፡፡ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ተመልሰው በመምጣት ተጨማሪ ፍተሻ በዋናው መኖሪያ ቤት መካሄድ እንፈልጋለን ብለው ሁለተኛ ዙር ብርበራ በምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ እናካሂዳከን በሚል ሰበብ ትንሹ ክፍል ውስጥ የጦማሪዋን እናት እነዲወጡ በማግለል ከማቀዝቀዛውን አንቀሳቅሰው አፍታም ሳይቆዩ 19 ገጽ የግንቦት ሰባት ፕሮግራም አግኝቻለሁ ሲል አንዱ ፈታሽ ተናግሯል፡።
የጦማሪዋን ወላጅ እናት እነዲፈርሙ ያግባቡ ቢሆንም ወላጅ እናትዋ ከክፍሏ እና ሌላም ቦታ በመፈተሽ ስታገኙ ያየሁት ወረቀት ላይ ፈርሜያለሁ ይህ ግን ምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ ያልነበረ እና እዚህ ያልተገኘ ሌላ ወረቀት ነው ሲገኝም አላየሁም በማለት አልፈርምም ብለዋቸዋል፡፡ በመሆኑም ፈታሾች ተጨማሪ የሰው ሃይል ደውለው በማስጠራት ለማግባባት ቢሞክሩም ስላልተሳካላቸው ይዘዋቸው የመጡትን የራሳቸውን ሁለት ምስክሮች ብቻ አስፈርመው ባለቤትዋ ለመፈረም ፍቃደኛ አይደሉም ብለው ቤቱን ለቀው ሄደዋል፡፡ ከፓሊስ ጋር የመጡት ምስክሮች አንደኛው አድራሻቸው በብርበራ ምስክርነት ዶክመንቱ ላይ ያልተጻፈ መሆኑንም ለመረዳት ችለናል ፡፡
በብርበራው ወቅት በነበራቸው የ7 ሰአት ቆይታ የጦማሪዋን መጸሃፍት የጉዞ ትኬቶች የስልጠና ማንዋል እና የመሳሰሉትን ጥቃቅን ወረቀቶች የወሰዱ ሲሆን ማብሰያ ክፍል ከፍሪጅ ጀርባ አገኘነው ካሉት ወረቀት ግን ቤት ውስጥ ያልነበረና ፓሊሶች ራሳቸው ያመጡት በመሆኑ እናትዋ ተናግረዋል፡፡
የዞን ዘጠኝ ጦማሪ አባላት ከየትኛውም በፓርላማ በአሸባሪነት ከተፈረጀ የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑና ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው እነዲሁም አነዚህ ድርጅቶች ላይ በተለያየ አጋጣሚ ትችቶቻቸውን ሲያቀርቡና ሲቃወሙ የሚታወቁ ቢሆንም ሲሆን በተያዙት አባሎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስገድዶ ለሃሰተኛ መረጃ እንዲፈርሙ የማድረግ ተግባር ሳያንስ ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ለማያያዝ ማስረጃን እንደተገኘ አድርጎ የማቅረቡ ተግባር መንግሰት ይታማበት የነበረውን የፓለቲካ ውንጀላን በሽብር የመቀየር ክስ በተግባር እንድናይ ያስቻለን ነው ፡።
በመሆኑም አሁንም ቢሆነ ጦማሪ ጓደኞቻችን ሃሳባቸውን በነጻነት ከመግለጻቸው ውጪ ምንም አይነት የወንጀልም ሆነ ሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው እያስታወስን መንግስት ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አንዲፈታ አሁንም አንጠይቃለን፡፡

Tuesday, May 13, 2014

Cooperation for Fragmentation: Reflection on Ethiopians Conceptualization of Freedom and Independence

I understand Ethiopians concept of freedom as to mean not to be restricted by others and not to be dependent on others. Since freedom is attained through community, we cooperate with others for the purpose of keeping our individual right to determine own actions. There is a relation between social co-operation and individual independence and freedom. In our case social cooperation is done for the purpose of ensuring our individual independence and right of doing whatever we love to do. We do not cooperate with those who do not respect our thoughts and actions. It is the individual and not the society which is the source of cooperation. If we want, we can scale up the individual right and independence to family,
community, ethnic and country levels. Injustice can easily be perceived, sensed and feel because we see no difference between us as individuals and the community we love. In scaling up process the essence is still the love for own freedom and independence, which is the mother of all kinds of social cooperation.
This habit of behavior and mindset has implication for economic development. Under the current Ethiopian economic situation and the state of the global economy, freedom means the right to specialization and interdependence. Cooperation is needed for interdependence and not for the promotion of individual independence. My view is that we find ourselves at a time in which the Ethiopian society needs organic cooperation and not the usual mechanical
cooperation grounded on the tradition of preserving individual independence.
I will try to ground my simple observation on empirical evidence which I analyzed in my research works. My first evidence comes from my current observation on the mechanism of economic progress in Ethiopia. Economic activities are chosen and organized in the Ethiopian society along the lines of two types of living organisms: rural households and firms in urban centers. The rural households are based on the land economy, while firms are based on capital/wage employment economy. I use the term living organism as a reference to underline their capability to response, self preserve, reproduce, grow and self-regulate in the process of resource creation and use in the society.
According to the recent 2012/13 agricultural sample survey of CSA (Central Statistical Agency) of Ethiopia, there are over 15 million agricultural households cultivating 17,5 million hectors of land. According to CSA definition “a household is considered an agricultural household when at least one member of the household is engaged in growing crops and/or raising livestock in private or in combination with others.” Be it a one person ousehold or a multi-person household (in fact over 90 percent is a multi person household), the person/s living in the household makes provision for their own living.
In rural Ethiopia households are a self-organizing beings. In my research I defined a household as a group of people who are organized themselves into families to occupy a separate farming and dwelling unit. Rural households are both a consumption and production units. The most important concerns of households is the security of household food supplies and cash needs. I have used different methods to standardize their consumption requirements and to estimate the quantity of resource needs. For example, a household can provide an average of four adult-equivalent labor and needs an average of four hector land to maintain the level of output needed for reproduction (an average of 12,8 quintal per subsistence household per year). The rural households are similar in purposes and live side by side. The question is what happens to their input and output proportional requirements and ratio as the their number increases over time.
Increase in Household Numbers in Rural Ethiopia, 1984-2013
As shown in Figure 1 in between 1984 and 2005 the household number increased by an average of 7,8% per year. Annually many new subsistence households are established and in a matter of one generation the number of agricultural households has more than doubled. The multiplication of the subsistence households increases the consumption requirements and land demand of the households and the number of subsistence labor. As their number and resource needs increases over time, the households intensified their co-operation for existence. The cooperation takes different forms including labor exchange, share cropping and land rent. For detailed empirical study you can down load our village report from http://people.su.se/~bmalm/Sodo.pdf.
As the household multiplied economic resources are fragmented and social cooperation is used as a means for peaceful existence of independent and self provisioning households. In cases where social cooperation could not manage the severity of resource scarcity, we observe armed conflicts, internal and international migration.
Experiences of other countries show that as the population growth pressure increases, there should be an increase in division of labor and specialization to introduce technology and increase labor productivity and mass production. What we observe in rural Ethiopia is the reverse: staunch effort to preserve the self provision mechanism and independent existence of the households. The EPDRF government is investing close to 15 billion Birr in this process of fragmentation with hope of changing the tide. What is at the root of all the household, however, is the freedom to be self sufficient (not to be dependent on others and not to be restricted by markets). What the evidence in the last 30 years show is that cooperation, coming from either the village or the state, nurtured the peaceful fragmentation of resources and household multiplications in the country. The household size numbering 15 million did not happen by miracle. Independent minded households received support from villages and governments. Rural household labor does not think what to specialize and how to be interdependent with others (market thinking). They prefer independence against the advantages of market interdependence.
My research experience in studying the habitual behavior of the business people and industrial firms is limited. Last year in Addis Ababa I presented a paper in a seminar and workshop on promoting industrial development in Ethiopia. I discussed about the construction of Special Economic Zones and Clusters and what Ethiopia can learn from Asian and European experiences. In a discussion following my presentation, a person whom claims to have many years of experience in the business sector and who himself is actively working for the promotion of the private sector in Ethiopia dismissed the relevance of cluster idea (geographical concentrations of economic and innovation activities) to Ethiopian conditions.
In my presentation I emphasized internal linkages, whereby cluster gains are furthered by local firm cooperation (joint action), local institutions and local social capital. Contrary to my model, the person underlined the need for industrial firms to work independently without trying to elaborate the advantages of operating in isolation. Since I understand the behavior of suspicion on claims and zero-sum cognition, I did not see any point in challenging his belief. I came to learn that I have to marshal a vast array of empirical evidence to convincingly argue about the advantages clusters in enhancing the individual capacities of small firms to access markets, acquire skills, knowledge, credit and information. I took it for granted that business people know from experience the advantages of connections between firms and institutions.
Political cases on the behavior of working independently or cooperating to work independently can be traced back to the Era of Princes (Zemene mesafint). By the beginning of the 19th century territorial aristocrats were dominant both in northern and southern Ethiopia. Kings were puppet in the hands of the territorial princes. For instance, King Tekle
Giorgis was dethroned six times in eleven years (1779-84, 1794-95, 1795-96, 1797-99, 1800). The territorial princes, though they were powerful, did not assume the title of King of Kings for practical reasons. Since regions were geographically very much interdependent, any expansion or contraction of a territorial power was at the expense of the neighboring power. Kings had to intervene to restrain and check conflicts among territorial powers. Kings had the ideological, traditional and legal grounds to intervene and restrain the territorial power. The Era of princes was the best political case of cooperation for fragmentation.
Emperor Tewedros, Yohannes and Menelik tried to standardized the system and created institutional interdependence and specialization. Their efforts of modernizing the political and military institution is currently interpreted as regional domination and ethnic subjugation. What is the point of “discovering the ethnic past” at a time when economic processes both at nation and globally level requires specialization and integration to promote technology and create mass production and employment.
The source lies in our habitual behavior to be independent and self reliance against all odds. What has happened to the multiplication of the rural households can happen to other instances. In fact those who advocate Ethiopian unity are also splintered into different political parties and they create forum or alliance (cooperation) to nurture their respective
organizational independence. Why? I do not mean that they should merge out of love; but I do not see the parties configuring what to specialize and how to be interdependent program wise.
Common to all Ethiopians including myself is the core habit of appreciating individual independence, no matter the level at which we project the idea. I am wondering why our mind remains static or fixed to this habit of “independence” no matter the costs while socioeconomic dynamic shifts overtime requiring new approaches and solutions? Global economy and consequences of population growth in Ethiopia require organic cooperation rather than mechanical cooperation used to nurture territorial/individual independence during the era of princes. In a country where I live (Sweden) administrative and economic actors are working hard to interconnect regions functionally thus making geographical division and administrative boundaries antiquated. Political parties are working on the idea and basis of “class struggle” to create unity among the people and create interdependence between party programs. What is the basis of our concept of freedom and independence? Is this concept fixed or relative changing with time? My view is that in a globalized world functioning on value chains and at a time of massive resource scarcity facing the Ethiopian people, freedom should lead to cooperation, specialization and interdependence.
I have not informally or formally discussed this idea with anyone and I apologize in advance for simplifying such sensitive issue.

Monday, May 5, 2014

TPLF/EPRDF’s Divisive and Polarizing Political Master Plan is the Problem: Addis Ababa Master Plan is simply the Symptom


The suffocatingly oppressive political rule of TPLF/EPRDF has continued to terrorize the people of Ethiopia, denying them their basic human rights to live in peace, dignity, and inclusive harmony. Since coming to power in 1991, the TPLF-led regime has implemented a deliberate system of permanent polarization and suspicion between and among communities. Obviously, the objective of this policy of permanent polarization and compartmentalized order is to weaken the ability of the Ethiopian people to resist and defeat this brutal totalitarian regime.Addis Ababa Master Plan
The genesis and history of TPLF/EPRDF is deeply tied with its addiction to violence, murder, torture, and mass terrorization. The events of the last two weeks in Addis Ababa, Ambo, and other parts of the country are a clear testament of TPLF/EPRDF’s violent nature and it’s disregard for the sanctity and dignity of human life. First, there was the arrest of nine Zone 9 bloggers for no other reason than reporting and speaking truth to power. These young members of Zone 9 are representatives of their generation, committed to taking their rightful place in history. They knew all too well that the regime’s intolerance and even disdain for press freedom could make them a prime target. However, these young budding journalists/bloggers continued to inform the public and expose the crimes of the regime to the world, even if it meant going to jail and facing all physical and psychological suffering that comes with imprisonment. Their arrest has reaffirmed the fact of the TPLF/EPRDF regime’s unflinching commitment to keeping the people of Ethiopia under its clenched fist, and their fear of what Zone 9 bloggers/journalists are doing to report and resist. As the bloggers/journalists have articulated, there are two types of prisons in Ethiopia: the notorious Makalawi (which is divided into 8 zones) and prison dungeons spread all across the county; and the open-air prison which is the entire country (and where the name Zone 9 comes from). The bravery of these young bloggers/journalists is a profound lesson to all who fight for democracy, freedom, and justice, and their message is clear – freedom is not free!
The other major event that took place over this past week is the demonstration and subsequent massacre of students at Ambo University in the western part of the country. The students were demonstrating against the TPLF/EPRDF proposed plan to expand Addis Ababa’s master plan into neighboring towns and localities. Like all of TPLF/EPRDF’s so called “development” and “ infrastructure building” projects, the expansion of the Addis Ababa master plan was received with suspicion and skepticism from the general public, as well as with the students at Ambo University and elsewhere. Truthfully, they have good reason to be suspicious because no project, no plan is hatched by TPLF/EPRDF without an ulterior motive that benefits their own inner circle and marginalizes vast majority of citizens. The so-called “New Addis Ababa Master Plan” could be another scheme by the regime to give members of their inner circle new business opportunities so that they can expand their economic and political control.
The broad daylight massacre of students at Ambo is in full violation of all laws, national and international, and is a fresh demonstration of the brutal and cruel nature of the regime that continues its reign of terror on the peaceful and law-abiding citizens. This endless state terrorism, however brutal and however cruel, has failed to break the will of the people. In the face of this indiscriminate state violence the Ethiopian people have continued to use every available means to voice their disapproval of the regime.
Despite this continued resistance for freedom, democracy, and justice, however, there is an observable weakness in how collective collaborations and partnerships are being fostered. It is a well-proven fact that compartmentalized concerns and group-based resistance hardly poses a strong threat to a regime as a brutal as TPLF/EPRDF. Throughout history, social justice and freedom movements only managed to achieve their objectives by building broad coalitions.
The growing bystander mentality because the issue is “theirs” not “ mine” in the end hands the weak and fragmented struggle to the oppressor. The leaders of all political entities resisting TPLF/EPRDF rule must be mindful that fragmented and self-contained resistance
only benefits the regime. In today’s Ethiopia, no group is spared from the wrath of TPLF/EPRDF terror except the inner circles of the regime and a select few. The masses of the Ethiopian people are victims and survivors excluded from participating in the political, economic, and social life of the country.
Those struggling for true democracy, justice, and freedom must realize that the purpose of a permanent polarization policy as designed and implemented by TPLF/EPRDF is to weaken and quash any possible collective resistance b y the people of Ethiopia. It is by building a strong coalition and by realizing that the destiny of those marginalized and brutalized by the regime are inseparable from one another, hence building a united front and presenting a united resistance, that Ethiopians can speed up the dream of living in a free, just, and democratic Ethiopia.
As we mourn the brutal massacre of students of Ambo University, as we agonize the arrest of Zone 9 bloggers/journalist and many others languishing in TPLF/EPRDF dungeons, let’s remember that piece-meal struggle that focuses only on “my” part of the house prolongs the regime’s life expectancy and extends the suffering of the people. In the end the people of Ethiopia must come together to address the root cause and problem of their two decades of suffering: the undemocratic, brutal rule of TPLF/EPRDF that capitalizes on its strategy of permanent polarization. It is time to wake up, and it is time to unite. The whole TPLF/EPRDF political master plan is the root of Ethiopia’s problem and that must be addressed first and foremost. As the old adage goes, unity is power!

Friday, May 2, 2014

BBC World News

Ethiopian security Forces opened fire during the Oromo students nonviolent protest rally at Western Oromia Ambo town. Eye witnesses said more than 30 people including 8 students killed and several wounded by security forces. The peaceful protestors opposing the alleged "Integrated Master Plan of Addis Ababa". The peaceful protest continued in a different Oromia region.

Wednesday, April 30, 2014

Ethiopia charges nine bloggers, journalists with inciting violence (Reuters)

zone9-e1398747809895
Ethiopia has charged six bloggers and three journalists with attempting to incite violence, their supporters said on Monday, prompting accusations from rights groups that the government is cracking down on its critics.
All nine defendants, including freelance journalists Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, appeared in court on Sunday after they were rounded up by police on April 25 and April 26, their colleagues told Reuters.
On Monday, Human Rights Watch (HRW) called on U.S. Secretary of State John Kerry, who visits Ethiopia on Tuesday, to press the government to “unconditionally release” all the defendants, but Addis Ababa dismissed the criticism of the case. “The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, HRW’s deputy Africa director. “The timing of the arrests – just days before the U.S. secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” she said in a statement. In 2012, Addis Ababa sentenced a prominent blogger and five other exiled journalists to between eight years to life on charges of conspiring with rebels to topple the government. In the new case, a colleague of Tesfalem said security officials in plain clothes searched his house and confiscated several materials before taking him to a detention center. An Ethiopian government official defended the case against the nine, saying it had nothing to do with muzzling the media. “CRIMINAL ACTIVITIES” “These are not journalists. Their arrest has nothing to do with journalism but with serious criminal activities,” Getachew Reda, an adviser to Prime Minister Hailemariam Desalegn, said. “We don’t crack down on journalism or freedom of speech. But if someone tries to use his or her profession to engage in criminal activities, then there is a distinction there,” Getachew told Reuters. Critics say Ethiopia – sandwiched between volatile Somalia and Sudan – regularly uses security concerns as an excuse to stifle dissent and clamp down on media freedoms. They also point to an anti-terrorism law, passed in 2009, which stipulates that anyone caught publishing information that could incite readers to commit acts of terrorism can be jailed for between 10 and 20 years. Addis Ababa says the law aims to prevent “terrorist attacks” as it is fighting separatist rebel movements and armed groups. A court in Addis Ababa adjourned the hearing for the group of bloggers and journalists until May 7 and 8. Kerry will meet Prime Minister Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa to discuss peace efforts in the region and to strengthen ties with Ethiopia, State Department spokeswoman Jen Psaki said in a statement. The State Department says the aim of Kerry’s African tour – which will also take in Democratic Republic of Congo and Angola – is to promote democracy and human rights.

Thursday, April 24, 2014

ነፃነት የጎደለው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ


            የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን በዝርዝር ተመልክቶ የገመገመ ተቃዋሚ ፓርቲ ከአንድነት በስተቀር ያለ 
አይመስለኝም፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች የዕቅዱን ግምገማ ውጤት ለህዝብ ለማድረስ ባለመቻሉ ግን ይህ የሚታወቅ 
ነገር አይደለም፡፡ ግምገማው የተከናወነው የተለያዩ ዘርፎችን ለሙያው ቅርበት ባላቸው ሰዎች በሚመሩት ሁኔታ 
ነው የተገመገመው፡፡ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን አንድ ክፍል ለመገምገም ሃላፊነት ከወሰዱት ሰዎች 
ውስጥ/አሁን ስም መጥቀስ አያስፈልግም/ ኢህአዴግ ይህን ዕቅድ ካሳካ ኢህአዴግ እሆናለሁ ማለታቸውን 
አሰታውሳለሁ፡፡ እኔ በግሌ ዕቅዱን እንደማያሳካ ሰጋቴን ባስቀምጥም እቅዱን ቢያሳኩትም ኢህአዴግ እንደማልሆን 
አውቃለሁ፡፡ እነዚህ ቁሳዊ ነገሮች የበዙበት ዕቅድ ነፃነቴን ለመውሰድ የተዘጋጀ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ የኢህአዴግ 
ደጋፊም አባልም መሆን የምቸገረው ኢህአዴግ የሚያራምደው አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለግለሰብ ነፃነት የሚሰጠው ቦታ ስለሌለ ወይም የይስሙላ ስለሆነ ነው፡፡ አሁንም አቋማችን መሆን ያለበት የእድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅድ የዜጎችን ነፃነት ቀምቶ የሚመጣ ከሆነ ባአፍንጫችን ይውጣ የሚል መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተቃራኒው የሚቆም መብቱ ነው፡፡ በህዳሴው ግድብ ከሚገኝ መብራት ኢትቪን እየተመለከተ ነፃነቱን በእልሙ ማየት ይችላል፡፡ ወይም በህዳሴው ግድብ መነሻ በሚፈጠር ማነኛም የስራ ዕድል ተጠቃሚ ሆኖ ነፃነት ድሮ ቀረ ብሎ የሌሎች ሀገር ዲሞክራሲን ማወደስ ሲሻው መሳደብ መብቱ ነው፡፡ ነፃነት በነፃ አይገኝም ብቻ ሳይሆን ነፃነትን ለፈለጉት ቁሳዊ ጥቅም አሳልፎ መሸጥ የግለሰቦች ምርጫ ነው፡፡ ነፃነት የሚገኘው በ “ምርጫ” ነው፡፡ ነፃ ለመሆን በመፈለግና ለዚህ ፍላጎት የሚከፈለውን ዋጋ በመክፈል የሚገኝ ነው፡፡ 
           እኛና ኢህአዴጎች የእድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅዱን በዕቅዱ ዘመን መጨረሻ ሰንገመግም እንዲሁም አቋም ስንይዝ በብርጭቆ ውስጥ እንደሚገኝ ውሃ “ግምሻ ሙሉ እና ግማሽ ጎዶሎ” በሚል ፍልስፍና መነፅር ኢህዴጎች ግማሽ ሙሉ እኛ ግማሽ ጎዶሎ እንደመረጥን ተደርጎ ቢወሰድ ልክም ተገቢም አይደለም፡፡ ኢህዴጎች ከአሁኑ እንደማይሆንላቸው ስላወቁ በዕቅድ ዘመኑ ከተቀመጡት “ወሳኝ ቁሳዊ ግቦች” ቢሆን ፈቀቅ ብለው፤ አሁን የደረሱበትን እና ወደፊት ያለውን “ተስፋ” በመመገብ ለቀጣይ ምርጫ እንደ ዋናኛ የምርጫ ግብዓት እየተዘጋጁ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት በዕቅድ የተቀመጡትን ግቦች ከማሳካት ይልቅ በዋነኝነት በፕሮፓጋንዳው ስለሚጠመዱ አሁን ከደረሱበት ብዙ ፈቀቅ እንደማይሉ ለመገመት አያስቸግርም፡፡ 

           የኢህአዴግ ሰዎች በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ በእያንዳንዱ ዘርፍ የተጣለው ግብ በዋና ዋናዎቹ ግማሽ ለመደረስ እንደማይቻል አመላካች ነገሮች እንዳሉ ይረዳሉ፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን አጠቃላይ ግቡ ሊሳካ ይቻላል ብለው ማመን መርጠዋል፡፡ ግማሽ ሙሉ ፍልስፍናን እንደመስፈርት እንደንጠቀም የሚገፉንም ለዚህ ነው፡፡ ለዚህም መከራከሪያ ብለው ያስቀመጡት በመሰረታዊ ዕድገት አማራጭ ከአስራ አንድ በመቶ በላይ እናድጋለን ብለን ነበር አሰር በመቶ ከዚያም ትንሽ ዝቅ ያለ ቢሆንም ዋናው ዕቅዱ የተለጠጠ ስለነበር ጥሩ ነበር ብቻ ሳይሆን እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል እንደሆነ ተደርጎ ስለሚነገረን መዘጋጀት ያለብን ይመስለኛል፡፡ ለምን? ቢባል መልሱ ባለ ብዙ ዘርፍ 
ነው፡፡ አንዱ በምክር ቤት ደረጃ ባሉ የኢህአዴግ አባላት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አልተሳካም ተብሎ በሚመጣ ጣጣ ከሞቀ /አንፃራዊ ነው/ ወይም ከአዲስ አበባ ኑሮ ወደ ወረዳ መውረድ ሊያስከትል ይቻላል፡፡ ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም እንዳሉት ወረዳ ወርዶ መስራት ቀላል አይደለም፡፡ ሌላው ደግሞ ይህ የተጠቀሰው ስጋት የብዙዎቹ ካድሬዎች ሊሆን ቢችልም ይህ ሰጋት የሌላቸው ጎምቶዎቹ ኢህዴጎች ግን የተንደላቀቀ የገዢነት ቦታ ላለማጣት የእድገትና ትራንስፎርሜሸን ዕቅድ በአብዛኛው ተሳክቶዋል በሚለው የመንግሰት ሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እኛንም እራሳቸውንም ለማሳመን መጣራቸው የማይቀር ነው፡፡ በኢህዴግ የሚዲያ አጠቃቀም ስትራቴጂ የተወሰኑ ሰዎች ሰለጉዳዩ የፈለገ ጥልቅ እውቀት ቢኖራቸው አጠቃላይ ህዝቡን በተለይም ለስልጣኝ መሰረቴ ነው የሚለው ድሃውን እስካታለለ ድረስ ስለ መረጃ ትክክለኝነት አይጨነቅም እና ለዚህ በሚደረግ ሽርጉድ እኛንም እውነት እስኪመስለን ድረስ ይህን እውሸት ልንሰማው መቻላችን በቅርብ ርቀት ያለ ሀቅ ነው፡፡ 

የዚህ ፅሁፍ መነሻ በቅርቡ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ሶስተኛ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ አሰመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት ቀርቦ ነበር፡፡ ሪፖርቱን ተከትሎ የኢህአዴግ አባላት የሚሰጡት አስተያየት ሪፖርቱን ያነበቡት አይመስሉም፡፡ ከሪፖርቱ ይዘት ይልቅ ቀልባቸውን የሳበው የኢቲቪ ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ሪፖርቱ በግልፅ ዋና ዋና የተባሉትና ዕቅዱ በቀረበበት ወቅት እነዚህ ዕቅዶች አሁን ባለ የፋይናንስ እና የመፈፀም አቅም የሚታሰቡ አይደሉም በሚል ትችት ሲቀርብባቸው የነበሩትን በሙሉ ለማሳካት የማይቻሉ እንደሆኑ አሳይቶዋል፡፡ ይህ ደግሞ ሲቀርብ የነበረው ትችት ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ የቀረበው ሪፖርት “በአጠቃላይ በመሰረተ ልማት ፕሮግራሞች አፈፃፀም ዙሪያ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሁለንተናዊ አቅም ማነስ፤ የመሰረተ-ልማት ግንባታና ማማከር አግልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ማነስ እና የፋይናንስ እጥረት ቁልፍ ማነቆዎች ሆነው ታይተዋል” ይላል፡፡ ሲጀመር እኛም ያልነው ኢህአዴግ በሚመራት ሀገረ ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሱት ዋና ግብዓቶች ማነቆ ስለሆኑ እንደዚህ ያለ የተለጠጠ ዕቅድ መሳካቱ ያጠራጥራል ነው እንጂ በዓለም ላይ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ የሰፈሩት ፕሮጀክቶ አይተገበሩም መተግበር የማይችሉ አስማት ናቸው አላልንም፡፡ አንባቢ ልብ እንዲልልኝ የምፈልገው በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን መጨረሻ የሀገራችን እድገት 11.2 በመቶ አማካይ ይሆናል 
የተባልነው፤ የኢንዱስትሪ/ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከ20 በመቶ በላይ፤ የአስፋልት መንገድ ሳይጨምር የገጠር ቀበሌዎችን ከዋና መንገድ ጋር የሚያገናኙ ከ71 ሺ ኪሎ ሜትር ክረምት ከበጋ የሚያገለግሉ መንገዶች ግንባታ፤ የአዲስ አበባን ቀላል ባቡር ግንባታን ሳይጨምር 2395 
 ግርማ ሠይፉ ማሩ 

Monday, April 14, 2014

ስለፍትህ ሲባል ስርዓቱ ይፍረስ! ክፍል 2 (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)


April 14, 2014
በዚህ ርዕስ ሥር ባለፈው ሳምንት በይደር ካቆየሁት ተከታይ ጽሑፍ በፊት አንድ እርምት የሚያሻው ጉዳይን በአዲስ መስመር ላስቀድም፡፡
ሬዲዮ ፋና እና “አምደኞቹ”
በ1988 ዓ.ም በኤፈርት ባለቤትነት ስርጭቱን አሀዱ ያለው “ሬዲዮ ፋና”፣ ከምስረታው አንስቶ ዛሬም ድረስ ልክ እንደ በረሃው ዘመን ሁሉ የሥርዓቱ ቀኝ እጅና የርካሽ ፕሮፓጋንዳው ማስተላለፊያ ቱቦ ሆኖ መዝለቁ ለወዳጅም ለጠላትም የማያከራክር ገሀድ የወጣ ሐቅ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተወሰኑ የግል ሚዲያዎች ላይ የርግማን ዘመቻ የታወጀ ይመስል ለተከታታይ ሳምንታት “ስመ-ጥር” ረጋሚዎችን ጣቢያው ድረስ ጋብዞ ማብጠልጠልና ማውገዙን ቀንደኛ ሥራው አድርጎ ይዞታል፡፡ በርግጥ ይህ ዘመቻ ከወራት በፊት በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የፕሬስ ድርጅት በኩል በ“ጥናት” ስም የወጣው ውንጀላ ቅጥያ ሲሆን፣ በቅርቡ ኢቲቪ ሰርቶ እንዳጠናቀቀው የሚነገርለት ዶክመንተሪ ፊልም ደግሞ “ሳልሳዊ” ዘመቻ ሆኖ ለጥቆ የሚቀርብ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡Journalist Temasegan Dasaleg
ሰሞነኛውን የፋና ዘመቻ ከተለመደው አቀራረብ የተለየ የሚያደርገው ከህወሓት ከበሮ መቺነት መሻገር የተሳነው ዛሚ ሬዲዮ ጣቢያን ከወከለው አቶ ዘሪሁን ተሾመ በተጨማሪ፣ የኢዴፓው አቶ ሞሼ ሰሙ እና የ‹‹ፎርቹ››ኑ ጋዜጠኛ ታምራት ወልደጊዮርጊስ በውጋ-ንቀል ስልት የርግማኑ ቡራኬ ሰጪ ሆነው መቅረባቸው ነው፡፡ ‹‹አዲስ አማኝ ከጳጳስ በላይ ልሁን ይላል›› እንዲሉ ሩቅ አላሚው የሕዳሴው ግድብ የሕዝብ ተሳትፎ አስተባባሪ ም/ቤት ምክትል ዳይሬክተር የሆነው ዛዲግ አብረሃም ሆነ ሚኒስትር ዴኤታው ሽመልስ ከማል የረከሰውን የአፈና መንፈስ ‹‹ለማቀደስ›› በቁርጠኝነት መሰለፋቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው፡፡ በርግጥ እነዚህ ሰዎች በቀጥታ ከስርዓቱ ህብስት ተቋዳሽ በመሆናቸው በዚህ ደረጃ ‹‹ማሸብሸባቸው›› ብዙም አያስገርምም፤ አስገራሚው ነገር ታምራት ወልደጊዮርጊስ ‹‹እንቁ›› እና ‹‹ፋክት›› መጽሔቶችን በአንድ ሰው የሚዘጋጁ አስመስሎ ከማቅረብም አልፎ፣ ማሕበረ ቅዱሳን የገጠመውን የመበተን አደጋን በተመለከተ የወጣውን ዘገባ እስከማውገዝ የደረሰበት ጽንፍ ነው፡፡
በወቅቱ ዛዲግ አብረሃ ሚዲያዎቹ እንዲደመሰሱ ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ፣ ታምራትም የማሕበረ ቅዱሳን አባላት ተቋማቸውን ከመንግስታዊ አፈና መከላከል እንዳለባቸው የምትመክረውን የ‹‹ፋክት›› ዘገባ ቃል በቃል ጠቅሶ ሲያበቃ ‹‹ቋቅ እያለኝም ቢሆን ከዛዲግ አብረሃ ጋር የምስማማበት ጉዳይ ይህ ነው›› በማለት ከፕሬስ አፈናው ጎን መቆሙን አስረግጦ ተናግሯል፡፡ በአናቱም መጽሔቶቹ ‹‹አብዛኛው ህዝብ የሚፈልገውን መርጠው የሚዘግቡ ናቸው›› ያለበት አውድ ነቀፋ ይሁን ምስጋና ግልፅ ባይሆንም፣ ቢያንስ አምባገነኑን በረከት ስምኦን እና ጋሻ-ጃግሬዎቹን ከማስደሰት፤ ብዙሃኑን ግፉአን ማገልገል የተሻለ ብቻ ሳይሆን የተቀደሰ ተግባር ስለመሆኑ በረከትም በልበ-ሙሉነት እሰጥ-እገባ ሙግት የማይሞክርበት ነጭ እውነት እንደሆነ ታምራት ቢያስተውለው የተሻለ ይመስለኛል፡፡ ግና፣ ሐቁ ይህ ቢሆንም ወንድም ታምራት ራሱ ብቻ ሙያውን አክብሮ የሚሰራ ጋዜጠኛ፤ ሌላውን ደግሞ ኃላፊነት የማይሰማው ከማድረጉም በዘለለ፣ እነዚህን ሚዲያዎች ከአርበኝነት ጋር አዳብሎ ለማውገዝ መሞከሩ የተኮረኮርኩ ያህል ሳልወድ በግድ ያሳቀኝ ጉዳይ ሆኖብኛል፡፡ ምክንያቱም በእኔ እምነት በኢትዮጵያችን ላለፉት ሁለት ዓስርታት ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ለሕግ የማይገዛ እና በሙስና የተጨማለቀ ሥርዓት ከመሆኑ አኳያ በጋዜጠኝነትም ሆነ በየትኛውም ሙያ ለሚንፀባረቅ አርበኝነት የተሻለው ብያኔ፣ ሀገርን ከፍርሰት መታደግ ማለት ነውና፡፡
ደግሞም በዚህች ሀገር ዝግመታዊ-ሞት ፊት ላይ ቆሞ የኮሪደር ሐሜቶችን ከመዘገብ በእጅጉ ለቆና ረቆ በመሻገር የውደቀታችን ምክንያት የሆነውን አገዛዝ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ማስወገድ ቅድሚያ የሚሰጠው ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ብዙ ጊዜ በእንዲህ አይነት ውይይቶች ላይ ሚዛናዊ ለመሆን ይሞክር የነበረው ታምራት (ለዚያኛውም አቋሙ በግሌ አመስግኘው አውቃለሁ)፣ ማሕበረ ቅዱሳንን በተመለከተ የወጡ ዘገባዎችን ባወገዘበት አዛው ሬዲዮ ጣቢያ ስቱዲዮ ውስጥ ተቀምጦ፣ ሽመልስ ከማል አንድ እንኳ የታሰረም የተሰደደም ጋዜጠኛ እንደሌለ ጠቅሶ አይኑን በጨው አጥቦ ሲከራከር ትንፍሽ አለማለቱ የቀራኒዮ መንገድ እና የንግድ ስራ ፍፁም የማይተዋወቁ ሆድና ጀርባ መሆናቸውን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
በነገራችን ላይ በዚህ ውይይት የአደባባይ ምሁሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ እና የኢትዮ-ምህዳሩ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ መሳተፋቸው ከሞላ ጎደል ከዘመቻው ጀርባ ያለውን ኢህአዴጋዊ ሴራ አጋልጦታል ብዬ አስባለሁና ባርኔጣዬን ከፍ አድርጌ አክብሮቴን ልገልፅላቸው እወዳለሁ፡፡ በተለይ ጉምቱ የፍልስፍና መምህር ዶ/ር ዳኛቸው፣ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብቶችን ብቻ ሳይሆን የሥርዓቱን ሃሳብ አልባነት ለመሞገት ለሚያደርገው አበርክቶ በድጋሚ አመሰግነዋለሁ፡፡…ከዚህ ሁሉ ሰበር ሐተታ በኋላ ወደ ክፍል ሁለቱ ዋናው አጀንዳችን ዘልቀን፣ በኢትዮጵያ ሰማይ ሥር ለፍትሕ መበላሸት የዳኝነት ሥርዓቱ ብቻ ሳይሆን ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግም የአንበሳውን ድርሻ ስለመውሰዳቸው ለማመልከት እሞክራለሁ፡፡
ፖሊስ ሲባል…
…የተወሰኑ የፌደራል ፖሊስ አባላት ዝሆን አድነው እንዲያመጡ በአለቃቸው ይታዘዛሉ፡፡ ከሰዓታት በኋላም ፖሊሶቹ ግዳያቸውን አምጥተው ለአለቃቸው ያስረክባሉ፡፡ ይሁንና አለቅየው ግዳያቸውን ባየ ጊዜ ባለማመን ዓይኖቹ ፈጥጠው ሊወድቁ ደረሱ፤ ለምን ቢሉ፣እሱ ያዘዛቸው ዝሆን፣ እነርሱ ያመጡት ግን ሁለት ጥርሱ የወለቀ፣ አንድ ቀንዱ የተሰበረ፣ አንድ አይኑ የጠፋ፣ ምላሱ የተቆረጠ… ብቻ ምን አለፋችሁ በድብደባ ብዛት ሊሞት የተቃረበ ፍየል ነበርና፡፡ እናም በቁጣ፡-
‹‹ዝሆን አይደል ወይ አምጡ ያልኳችሁ?›› ሲል ያፈጥባቸዋል፤
‹‹ጌታዬ፣ ዝሆን ነኝ ብሎ እኮ አምኗል!›› በማለት ቆፍጣና ፖሊሶቹም በሕብረት መለሱለት፡፡
…ይህችን ቀልድ ለዚህ ንዑስ-ርዕስ መግቢያ ያደረኩት፣ በነባሩ ባሕል እንዲህ ያሉ ጉዳዮች በቀልድ፣ በግጥም፣ በምሳሌዊ አባባል… መገለፃቸው የተለመደ ከመሆኑ አኳያ ስለሀገራችን የፖሊስ አባላት ስንነጋገር ከቀልዷ ጀርባ መራራ እውነት ማድፈጡን አምነን እንድንቀበል ገፊ-ምክንያቶች በመኖራቸው ነው፡፡
እንደሚታወሰው በየትም ሀገር የተፈፀመ ወንጀል ከዐቃቤ ሕግም ሆነ ከፍርድ ቤት በፊት በፖሊስ የምርመራ ሂደት ውስጥ ማለፉ የግድ ነው፡፡ የዘርፉ ምሁራን ‹‹የፖሊስ ምርመራ ሳይንስ ነው›› እንዲሉ ሙያው ክህሎት የሚጠይቅ መሆኑ አይካድም፡፡ ይሁንና ተጨባጩ እውነታ የሚነግረን የ83ቱን የመንግስት ለውጥ ተከትሎ በዘርፉ እንዲሰማሩ የተደረጉት አብዛኞቹ መርማሪዎች ድርጅቱን ለቡሕተ-ሥልጣን ያበቁ ታጋዮች መሆናቸውን ነው፡፡ በርግጥም በረባውም ባልረባውም ወንጀል ተጠርጥሮ እጃቸው የገባውን ሁሉ አፈር-ድሜ በማስጋጥ የ‹‹ሚመረምሩበት›› መንገድ ኩነቱን ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ ይህ ሁናቴም ይመስለኛል የፖሊስን ሙያ ከሳይንሳዊ ጥበብ ወደ አሳረ-ፍዳ ማሳያ አውርዶ የተጠላ ያደረገው፡፡ ለዚህም ኩነና በርካታ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡ የሩቁን ትተን የቅርቡን እንኳ ብንመለከት የህዝበ-ሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ችሎት ላይ ቀርበው በማዕከላዊ ምርመራ እስር ቤት መርማሪ ፖሊሶቹ ሰብዓዊ መብቶቻቸው ተገርስሶ ሲያበቃ ምን ያህል አካላዊና መንፈሳዊ ስቅየት እንደደረሰባቸው ከተናገሩት መሀል የሚከተሉትን በዋናነት እናገኛለን፡-
‹መርማሪ ፖሊሶቹ እንቅልፍ ከልክለው የተዳከመ አካልን ልብስ አስወልቆ እርቃን በማስቀረት መግረፍ፣ የዘር ፍሬ ብልት ላይ በውሃ የተሞላ ጠርሙስ ማንጠልጠል፣ በኤሌክትሪክ ገመድ የውስጥ እግርን መግረፍ፣ ጢምን በአሰቃቂ ሁኔታ መንጨት፣ እጅና እግርን ሰብዓዊነት በጎደለው መልኩ ለረጅም ሰዓታት ማሰር፣ ጭንቅላትን በቆሸሸ ውሃ ውስጥ መንከር፣ ከ24 ሰዓታት በላይ ቀጥ ብሎ እንዲቆሙ ማስገደድ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ሾክ ማደረግ እና የመሳሰሉት፡፡› በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማትም በተደጋጋሚ ጊዜ በተለይም ከደርግ ስርዓት ጀምሮ ዋነኛ ማሰቃያ በሆነው ማዕከላዊ የምርመራ ጣቢያ የሚፈፀመውን ተግባር በሪፖርት መልክ ማውጣታቸው ይታወሳል፡፡ ከወራት በፊት ሂዩማን ራይትስ ዎች ይህንን የስቃይ ጣቢያ አስመልክቶ ‹‹They want a confession: Torture and Ill-treatment in Ethiopia’s Makelawi Police Station›› በሚል ርዕስ ባሰራጨው ሪፖርት በጣቢያው የሚፈፀመውን ግፍ ከመግለፁም በተጨማሪ፣ ታሳሪዎች እንዴት ባለ ሁኔታ ‹‹የእምነት ቃል››እንደሚሰጡ አመላክቷል፡፡ ለማሳሌም አንድ ስሙ ያልተጠቀሰ፤ ነገር ግን በጣቢያው ታስሮ የነበረ ሰው ገጠመኝን ከሪፖርቱ እንደሚከተለው ልጥቀሰው፡-

‹‹ወደ ጣቢያው የገባሁ ቀን ኢ-ሜይል አድራሻዬን ከነምስጢር ቁልፉ እንድሰጣቸው ጠየቁኝ፤ ሰጠኋቸው፡፡ በውስጡም ምንም አይነት የፖለቲካ አንድምታ ያለው መልዕክት አልነበረም፡፡ ይሁንና ከሶስት ቀን በኋላ በዛው አድራሻዬ ‹ከኦነግ የተላከ መልዕክት ተግኝቷል› ብለው ጠየቁኝ፡፡ ሆኖም ነገሩን እንደማላውቅ እያወቁ ‹ለእኔ የተላከ መልዕክት ነው› ብለህ ፈርም ሲሉ አዘዙኝ፡፡ እኔም ከታሰርኩ በኋላ የተገኘ በመሆኑ አልፈርምም አልኩ፡፡ በዚህም የተነሳ ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመውብኛል፡፡››
በርግጥም የሀገሪቱን የወንጀል ምርመራ ስራን ተነቃፊና ተወጋዥ ያደረገው በእውቀት ማነስ፣ በስቅየት (በቶርቸር) እና በሙስና የተተበተበ መሆኑ ብቻ አይደለም፡፡ በአደረጃጀቱም ነው፤ ለምሳሌ ከፌዴራልና ክልል ፖሊስ በተጨማሪ ግምሩክ የራሱ እስር ቤት፣ የራሱ መርማሪና ዐቃቢ-ሕግያን አሉት፡፡ ፀረ-ሙስናም እንዲሁ የጠረጠረውን ሁሉ አስሮ ይመረምራል፤ ይከስሳልም፡፡ አንዳንድ ምንጮቼ እንዳቀበሉኝ መረጃ ከሆነ ደግሞ በሽብር ጉዳይ የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን (ቡድኖችን) ራሱን ችሎ አስሮ የሚመረምር እና የሚከስ ተቋም በቅርቡ በአዋጅ ሊቋቋም ዝግጅቱ ተጠናቅቋል፡፡ እንግዲህ እነዚህ ሁሉ መዋቅራዊ ትስስር በሌለው ሁኔታ በፖሊስ ስራ የመሰማራታቸው ምስጢር፣ አንድም ሳይንስ እንጂ አሳር ዕውቀት ባለመጠየቁ፣ ሁለትም ንፁሀንን ከወንጀለኛ ጋር ደባልቆ ለመውቀጥ ስለሚመች፣ ሶስትም ስርዓቱ ተቀናቃኞቹን ለመደፍጠጥ በ‹‹ሕጋዊ አሠራር›› ሽፋን ተጨማሪ ጡንቻ እንዲኖረው ማስቻሉን በማስላት ይመስለኛል፡፡ በዚህ አይነት ምርመራ የተገኙ መረጃዎችም ፍርድ ቤት ቀርበው እንደሕጋዊ ማስረጃ እየተቆጠሩ እስከ ዕድሜ ልክ የእስር ቅጣት ሲያስበይኑ ደጋግመን ተመልክተናል፡፡
ይህም ሰፊው ሕዝብ በፍርሃት እየተርበደበደ ሰጥ-ለጥ ብሎ እንዲገዛ፤ አሊያም እንደ ጥንቸሊቷ አገር ጥሎ እንዲጠፋ ለማድረግ ያለው ጉልበት በግልፅ ተተግብሮ የታየ የሥርዓቱ የዕለት ተዕለት ምግባር ነውና ከዚህ በላይ ትንታኔ አያሻውም፡፡ ከዚህ ይልቅ የጥንቸሏ አፈ-ታሪክ ተብሎ የሚነገረው ነባራዊ እውነታውን በሚገባ ያንፀባርቃልና እንደወረደ ልጥቀሰው፡-…ከለታት አንድ ቀን አንዲት ጥንቸል ከመጣባት የመዓት ናዳ ማምለጥ የምትችለው ቀዬዋን ጥላ ስትሰደድ እንደሆነ ብቻ በማመኗ ልቧ እስኪፈነዳ ድረስ ጋራ-ሸንተረሩን እያቆራረጠች ስትሮጥ ድንገት ከሀገሪቱ ድንበር አጠገብ ከሚኖር አንድ ግድንግድ ጦጣ ጋር ፊት-ለፊት ተፋጠጠች፣ በድካም ዝላም ቁና ቁና እየተነፈሰች ‹‹ይህ ጦጣ ፖሊስ ይሆን እንዴ?›› ብላ እየተጠራጠረች ማምለጫ ዘዴ ስታውጠነጥን፣አያ ጦጣ፡- ‹‹ወይዘሪት ጥንቸል፣ ለመሆኑ ምን የከበደ ጉዳይ ቢገጥምሽ ነው እንዲህ ልብሽ እስኪፈርስ ድረስ የምትሮጪው?›› ሲል ይጠይቃታል፤‹‹የዝሆን ዘር በሙሉ ከያለበት ተለቅሞ በቁጥጥር ስር እንዲውል አስቸኳይ ትዕዛዝ መውጣቱን እስካሁን አልሰሙም እንዴ?›› ብላ በጥርጣሬ ትክ ብላ እያስተዋለችው ጥያቄውን በጥያቄ ስትመልስለት፣
አያ ጦጣ፣ እጅግ በጣም ከመደነቁም በላይ ግራ ግብት እያለው ‹‹ታዲያ አንቺ ምን አገባሽ፤ ዝሆን አይደለሽ?›› ሲል መልሶ ይጠይቃታል፤ ‹‹ወይ አያ ጦጣ! ዝሆን ባልሆንስ?! አለመሆኔ ተጣርቶ እስክለቀቅ ድረስ ለምን ብዬ ታስሬ ልገረፍ? ደግሞስ በዱላ ብዛት ዝሆን ነኝ ብዬ ያመንኩ እንደሆነ መጨረሻዬ ምን ሊሆን እንደሚችል አስበውታል? ይልቅ እርስዎም አይሞኙ! በጊዜ አብረውኝ ከመዓቱ ዘወር ብለው ቢቆዩ ይሻሎታል፤ ኑ እንሂድ›› ብላ በፍርሃት የተዋጠችው ምስኪኗ ጥንቸል ሩጫዋን ቀጠለች፡፡ …በእኛይቱ የመከራ ምድርም፣ እኛና ኢህአዴግ በዚህ ደረጃ ፍፁም የማንተማመን፣ በጎሪጥ የምንተያይ ሆነን ከቀረን እንደ ዘበት ሃያ ምናምን አመታት ተቆጥረዋል፡፡
ዐቃቢ ሕግ ሲባል….
በዚህ አውድ ሌላው ተጠቃሽ ተቋም፣ ፖሊስ በ‹‹የትም ፍጪው…›› መንገድ ያመጣለትን ‹‹መረጃ›› ሳያላምጥ በመዋጥ ለክስ የሚያበቃው ዐቃቤ ሕግ ሲሆን፣ ለአጠቃላዩ የፍትሕ መዛባትና መጨማለቅም በዕኩል ደረጃ ተጠያቂ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡
ለአደባባይ ያልበቁ አያሌ የዐቃቢ-ሕግያን ሸፍጦችን ትተን በድህረ ምርጫ 97 የተከሰተውን አለመግባባት ተከትሎ ለእስር ከተዳረጉት የቅንጅት ለአንድነትና ለፍትህ ፓርቲ አመራሮች ጋር የተያያዘውን እንመልከት፡፡ እንደሚታወሰው መጀመሪያ የቀረበባቸው ክስ ‹‹የዘር ማጥፋት›› የሚል የነበረ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያን በተመለከተ ለረዥም ዓመታት ጥናት ያደረገው አሜሪካዊ ፕ/ር ዶናልድ ሌቨን፣ አቶ መለስን ‹‹ዘር ማጥፋት እኮ ቀልድ አይደለም›› በማለት አጥብቆ ከወቀሰው በኋላ ክሱ ‹‹ሕገ-መንግስቱን በኃይል የመናድ እና ዘር የማጥፋት ሙከራ›› ወደሚል መቀየሩን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ይናገራሉ፡፡
የሆነው ሆኖ ጉዳዩ ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት ዐቃቢ-ሕግያኑ በተከሳሾቹ ላይ በ‹‹ማስረጃ››ነት ካቀረቡት ሰነዶች መካከል የአባላዘር በሽታ የህክምና ምርመራ ወረቀትን ጨምሮ፣ ሀሰተኛ (ፎርጅድ) ደብዳቤዎች እና ከክሱ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላቸው የቪዲዮ ፊልሞች እንደነበሩ አይዘነጋም፡፡ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› በሚለው መጽሐፉ፣ በጥቅምት 25/1998 ከ‹‹አዲስ አበባ ፖሊ ከፍተኛ ክሊኒክ›› ቢኒያም (የአባቱም ስም ተጠቅሷል) ለተባለ ሰው የአባላዘር ምርመራ አድርጎ የተሰጠው የሕክምና ምስክር ወረቀት ‹‹ሕገ-መንግስቱን በኃይል ለመናድ ሞክረዋል›› በተባሉት የቅንጅት መሪዎች ላይ በ‹‹ማስረጃ››ነት መቅረቡን ከመጥቀሱም በላይ ሰነዱን በገጽ 444 ላይ እንዳለ በማተም ለታሪክ ምስክርነት አብቅቶታል፡፡ መቼም ይህ ሁናቴ አቶ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ጦር ሶማሊያን የወረረው የአሜሪካንን ተልዕኮ ለማስፈፀም ነው? ተብሎ ለቀረበበት ወቀሳ አከል ጥያቄ፣ አሜሪካ የምትሰጠው ዕርዳታ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን መከላከል ላይ ያተኮረ እንደሆነ ከገለፀ በኋላ ‹‹ሶማሊያ ውስጥ ደግሞ በኮንዶም አንዋጋም!›› ብሎ እንደመለሰው አይነት ቧልት አቅልለን እንዳናልፈው የሚያግደን ጉዳዩ ‹‹አንድ ንፁህ በሀሰት ከሚፈረድበት፣ ሺ ወንጀለኞች በነፃ ቢለቀቁ ይመረጣል›› ከሚባልለት ፍትሕ ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ነው፡፡
በጥቅሉ ላለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ ለእስር የተዳረጉ ንፁሀንም ሆነ በሙስና የተወነጀሉት ላይ እየቀረበ ያለው ክስና ማስረጃዎችን ሥራዬ ብሎ ለመረመረ ሰው፣ የፍትሕ መዛባቱን ደረጃ ፍንትው አድርገው ያሳዩታል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለምሳሌም ከወራት በፊት ‹‹በገቢዎችና ግምሩክ ባለሥልጣን የአ/አ ኤርፖርት ቅ/ጽ/ቤት የመንገደኞች ጓዝ የሥራ ሂደት መሪ›› ባለሥልጣን ላይ የተመሰረተውን ክስ ብናየው እንዲህ የሚል ሆኖ እናገኘዋለን፡-
‹‹ከአሜሪካና ከአውሮፓ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ መንገደኞች ዕቃዎቻቸውን አስፈትሸው ቀረጥና ታክስ ሊከፈልባቸው የሚገቡት ላይ መክፈል እንዳለባቸው ኮንትሮባንድም ከሆነ እንደሚወረሱ እያወቀ ማንነታቸውና ብዛታቸው ያልተለዩ መንገደኞች ዕቃቸው እንዳይፈተሽ ማድረግ፡፡››
መቼም ይህ አይነቱ ክስ በምድራችን የመጀመሪያው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ማንነታቸውና ብዛታቸው፣ ቀኑና ወሩ ተለይቶ ባልታወቀበት ጊዜ ከመንገደኞች ጋር በመመሳጠር የተሰራ ወንጀል አለ ብሎ ክስ መመስረት ከጥንቆላ በምንም ሊለይ አይችልምና ነው፡፡ ኧረ ለመሆኑስ! የሰዎቹ ቁጥርና ያስገቡት የዕቃ ዓይነት ካልታወቀ ባለሥልጣኑ ‹‹ፈፀመ›› በተባለው ሙስና ሀገሪቱ ከቀረጥ ማግኘት የነበረባትና ያሳጣት ገቢ ምን ያህል ነው? አንድ ብር? አንድ ሺህ? አንድ ሚሊዮን ወይስ አንድ ቢሊዮን? ይሁንና የተከሳሽ ጠበቆች ክሱ በዚህ መልኩ መቅረቡን በፍርድ ቤት በመቃወማቸው ዐቃቢ ህግ አሻሽሎ እንዲያቀርብ ይታዘዛል፡፡ ተሻሽሎ የቀረበው ደግሞ ባጭሩ እንዲህ ይጠቀሳል፡-
‹‹ቀኑና ወሩ ተለይቶ ባልታወቀበት በ2002 ዓ.ም ዜግነታቸው አሜሪካዊ የሆነ ሁለት ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ሁለት ሻንጣ የመኪና መለዋወጫ ከተያዘባቸው በኋላ አስለቅቋል፡፡ ግንቦት 24 ቀን 2003 ዓ.ም የሰንሻይን ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ ሳሙኤል ታፈሰ ከዱባይ ሀገር ያስገቡት የመኪና መለዋወጫ ዕቃ እንዲያልፍ ሲያስደርግ በሌላ ባልደረባው ተይዟል፤ ከሐምሌ ወር 2002 ዓ.ም እስከ ነሐሴ ወር 2003 ዓ.ም ከጠዋቱ አንድ ሰዓት እስከ አራት ሰዓት ባለው ጊዜ ከተለያዩ ሀገራት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ መንገደኞች ሠልፍ ይዘው እያለ ከዚህ መለስ ያሉት መንገደኞች ሻንጣቸውን ሳያስፈትሹ፣ ቀረጥና ታክስ ሳይከፍሉ እንዲያልፉ ማድረግ፡፡››
እነሆም እውነት እውነት እላችኋለሁ፣ ሀገሪቱ እንዲህ ባሉ የሕግ ባለሙያዎች ስር ወድቃለችና ‹እግዚኦ በሉ›፡፡ እግዚኦታው ግን የሁለቱ እንስቶች ስም እና ያሳለፉት ዕቃ ተመን ባለመታወቁ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በጽሁፍ በቀረበ ክስ ላይ ከሠልፈኞቹ መካከል ‹‹ከዚህ መለስ ያሉት መንገደኞች…›› ተብሎ ድፍን ያለ ነገር ‹‹መረጃ›› ሆኖ መቅረቡ ነው፡፡ ግና፣ ይህ ምን የሚሉት መረጃ ነው? ያውም ለፍርድ ቤት! እናም ጥያቄያችን እንዲህ እያለ ይቀጥላል፡- የትኛው ሠልፍ ጋ ያሉ መንገደኞች ናቸው በሕገ-ወጥ መንገድ ያለፉት? የቀኙ? የመሀለኛው? የግራው? የሠልፉስ ርዝመት ምን ያህል ነው? የሠልፈኞቹስ ብዛት? አምስት? ሀምሳ ወይስ አምስት መቶ? በርግጥ ክሱ ለአንዱም ጥያቄያችን ምንም አይነት ምላሽ አይሰጥም፡፡ ጉዳዩን ይበልጥ የሚያወሳስበው ደግሞ ይህ ‹ሾላ በድፍን› የሆነ ወንጀል የተፈፀመው ከሐምሌ ወር 2002 ዓ.ም እስከ ነሐሴ ወር 2003 ዓ.ም ድረስ በየቀኑ መሆኑ ነው፡፡ መቼም እነዚህ ሁሉ ጉዶች እውነት ከሆኑ በዚህች ሀገር፣ ማፍያ እንጂ መንግስት አለ ብሎ የሚመሰክር ደፋር ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡
በጥቅሉ የፖሊስም ሆነ የዐቃቢ-ሕግያኑና የዳኞቹ እንዲህ ሙያውን እና ተቋሙን የማራከስ አካሄድ ከአንድ ገፊ-ምክንያት የዘለለ ሌላ መነሾ የምናገኝለት አይመስለኝም፡፡ ይኸውም ሥልጣኑን ለማራዘም ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሰው ኢህአዴግ፣ በዋናነት ዋስትና የሚሆኑትን ፖሊስ፣ ዐቃቢ-ሕግ እና ፍርድ ቤቶችን በታጋዮች እና በካድሬዎች በመሙላት፣ በተለየ የፖለቲካ አቋም ከፊቱ የሚቆሙትን እየጨፈለቀ ለማለፍ አስልቶ የቀመረው በመሆኑ ነው፡፡
ኦርዌላዊ ስርዓት
የዚህን ስርዓት ቅጥ ያጣ አምባገነንነት ማብራራት አድካሚ እየሆነ ነው፡፡ የሚፈርሰው ማህበራዊ ዕሴት፣ የሚናደው ሀገራዊ ማንነት፣ እንደ አምባሻ የሚቆራረሰው መሬት፣ አልፎ ተርፎም እየጠፋ ያለው ትውልድ እና መሰል ጉዳዮችን ጠቃቅሶ፣ የነገይቷ ድህረ-ኢህአዴግ ኢትዮጵያ በገዢው ስብስብ ክፉ መዳፍ ሳቢያ ህልውናዋ ከገደሉ ጠርዝ ላይ ስለመቆሙ ማተት መደጋገም ነውና እንለፈው፡፡ ይህም ሆኖ ግን አገዛዙ በፍትሕ ስርዓቱ በኩል የሚያካሂዳቸው ዘግናኝ ድርጊቶች የመዓቱን ጊዜ ቅርብ የሚያደርጉ መሆናቸውን ማስታወስ (የሚሰማ ባይኖርም) የዜግነት ግዴታ ይመስለኛል፡፡ የአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ፣ ቁጥራቸው የበዛ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት በተደጋጋሚ እንደዘገቡት፣ የዚህች አገር ምስኪን ልጆች በማይታወቁ ድብቅ እስር ቤቶች ጭምር መከራ እየወረደባቸው ነው (እኔ ይህንን ጽሑፍ በማዘጋጅበት፣ እናንተም አሁን በምታነቡበት ሰዓትም ቢሆን ለይተን በማናውቃቸው በርካታ የስቃይ እስር ቤቶች፣ በእልፍ አእላፍ ወገኖቻችን ላይ ግፍ እየተፈፀመ መሆኑን መካድ አይቻልም)፡፡
እነዚህ ማሰቃያ ቦታዎች ከምስራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከደቡብ እስከ ሰሜን ባሉት የሀገሪቱ አካባቢዎች ተሰበጣጥረው የተዘጋጁ ናቸው፡፡ በነዚህ ካምፖችም የሚታጎሩት ዜጐች በዋነኝነት ከገዢው ግንባር የተለየ (የሚቃረን) ፖለቲካዊ አመለካከት ያላቸው ስለመሆኑ የተቋማቱ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፡፡ በተለይም ብረት አንስተው የሚታገሉ ኃይሎች የተነሱባቸው ክልል ተወላጆችን ማሰቃያ ካምፖቹን የሚያደልቡ ‹የተመረጡ› መከረኞች ሆነዋል፡፡ ኢህአዴግ እንጥፍጣፊ ለሕገ-መንግስቱ አክብሮት ቢኖረው፣ የዜጎቹ ወንጀሎች የቱንም ያህል ቢከፉም እንኳ፣ በግልጽ የፍርድ ሂደት ተገቢ የሆነ ተመጣጣኝ ቅጣት ማግኘት በተገባቸው ነበር፡፡
የዚህ አይነቱን የፍትህ ምኩራቡ አስፀያፊ እርክስናን፣ በግላጭ የሚያሳየን ሌላኛው ጭብጥ በኦጋዴናውያኑ ላይ እየወረደ ላለው ግፍ ተጠያቂ ተቋምም ሆነ ባለሥልጣን እስካሁን ድረስ አለመኖሩ ነው፡፡ የስዊድናውያኑን ሁለት ጋዜጠኞች መታሰርና በይቅርታ መፈታት ተከትሎ፤ በክልሉ ያለው ፍርድ ቤት ስለማያውቀው ዝርፊያ፣ እስርና ግድያ በምስልና በድምፅ የተደገፉ ማስረጃዎች ከጥቂት ወራት ወዲህ ተሰምተዋል፡፡ የአካባቢው የቀድሞ ባለስልጣን ወደስዊድን በተሰደደ ማግስት ያቀረባቸውን እነዚህን ማስረጃዎች ኢህአዴግ እንደለመደው የኦብነግ ከንቱ ውግዘት አድርጎ ማለፍ አይቻለውም፡፡ በዚህ ሰው ማስረጃም ሆነ ክልሉን ባጠኑ ምሁራንና ተቋማት ዘገባዎች መሰረት የጠቀስኳቸው ዘግናኝ ክስተቶች ማህበረሰቡን እየናጡት ነው፡፡
በተለይ ልዩ ሚሊሺያ የሚባለው ሕገ-ወጥ ሀይል፣ በሱማሌ ክልል ጎዳና ላይ ያሻውን እያነቀ እንዲያስር፣ ልጃገረዶችን እንዲደፍር፤ ገፋ ካለም በጥይት አረር እንዲረሽን የተተወበት አግባብ የሚመሰክርልን የፍትሕ ስርዓቱ ድምጥማጡ ስለመጥፋቱ ብቻ ነው፡፡ በዚህ መልኩ በሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች ካለዘውግ፣ ሐይማኖት እና ዕድሜ ልዩነት፤ ካለፍርድ ቤት እውቅና እየተፈፀመ ያለው ግፍ፣ የፍትህ ተቋሙ የዜጎችን ህልውና ለመጨፍለቅ ከገዢዎች ጋር በጥብቅ የተጋመደ ስለመሆኑ ያስረግጡልናል፡፡ እንግዲህ ፍትሕና ርትዕ የሰማይ ላይ ሩቅ ተስፋዎች እንዲሆኑብን የፈቀደውን ስርዓት እስከ መቼ መታገስ ይቻለናል? ስለርትዕ በኢትዮጵያ ምድር ላይ መስፈን ሲባልስ፤ የኢህአዴግን ቅፅር በህዝባዊ ሰላማዊ አብዮት ብንንደው፣ መስዋዕትነታችን ሀገርን ከመዓት ለማዳን ሲባል በፈቃደኝነት የሚከፈል ትውልዳዊ ግዴታ አይደለምን?! (በቀጣዩ ከአራጣ ማበደር ወንጀል እስከ መንግስታዊ ሙስና ላሉ ጉዳዮች እና ለፍትሕ ሥርዓቱ ሞቶ መቀበር ማሰሪያ አበጅቼ አጀንዳውን ለጊዜው እደመድመዋለሁ)
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
አዲስ አበባ